Soggetto 1: Rinasce d'acqua e di Spirito
1-7. ሮሜ 8፡30 እንዲህ ይላል፡- ‹‹አስቀድሞም የወሰናቸውን እነዚህን ደግሞ ጠራቸው፤ የጠራቸውንም እነዚህን ደግሞ አጸደቃቸው፤ ያጸደቃቸውንም እነዚህን ደግሞ አከበራቸው፡፡›› ታዲያ ይህ ምንባብ በሒደት የሚሆን ቅድስናን ይደግፋልን?
ይህ ምንባብ በሒደት ስለሚሆን ቅድስና አያስተምርም፡፡ ብዙ የሥነ መለኮት ምሁራንና ሐሰተኛ ሰባኪዎች ‹‹በኢየሱስ የሚያምኑ ሰዎች ቀስ በቀስ ይለወጡና በሥጋና በመንፈስ ሙሉ በሙሉ ይቀደሳሉ›› ብለው አስተምረዋል፡፡ ብዙዎችም ይህንን አምነዋል፡፡
እንደ እውነቱ ከሆነ ግን ገና ዳግም ያልተወለዱ ክርስቲያኖች ራሳቸውን ይበልጥ ግትር ሆነው ያገኙታል፡፡ በልባቸው ውስጥ ያለው ሐጢያት እያረጁ ሲሄዱ ያድጋል፡፡ ቅድስናችን እንዴት በጊዜ ላይ የሚመሰረት ሊሆን ይችላል? ‹‹በሒደት መቀደስ›› የሚሉት ቃሎች እግዚአብሄር አብዝቶ የሚጠላቸውና ዲያብሎስም ሊጠቀምባቸው የሚወዳቸው ቃሎች ናቸው፡፡
እኛ ጻድቃን መሆን የምንችለው በራሳችን መውጪያ መንገድ በማይኖረን ጊዜ ነው፡፡ ኢየሱስ በጥምቀቱ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ስላስወገደና ለእነርሱም ዋጋ ለመክፈል ራሱን መስዋዕት ስላደረገ ጽድቃችን የተመሰረተው በኢየሱስ ጥምቀትና ደም ላይ ብቻ ነው፡፡ ኢየሱስ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ በራሱ ላይ በመውሰዱ እውነታ ላይ ባለን እምነት አማካይነት ጻድቃን ሆነናል፡፡
‹‹ቅድስና›› የሚለው ቃል ‹‹ቅዱስ መሆን›› ማለት ነው፡፡ በራስ ቅዱስ ለመሆን መሞከር በእውነት ማመን ሳይሆን በራስ ደካማ ሥጋ መታመን ነው፡፡
ቀስ በቀስ በሚሆን ቅድስና ላይ ተስፋ ማድረግ የሚመጣው ከራሳችን መንፈሳዊ ፍላጎቶች ነው፡፡ እያንዳንዱ ሐይማኖት የራሱ የሆነ የቅድስና ቃል አለው፡፡ ነገር ግን እኛ በኢየሱስ የምናምን ሰዎች በቃሉ ላይ ፈጽሞ ጠቀሜታን ማኖር አይገባንም፡፡
በኢየሱስ በማመን ቀስ በቀስ አንቀደስም፡፡ የመንፈሳዊ ግርዘት እውነት በሆነው የኢየሱስ ጥምቀትና ደም በማመን ለአንዴና ለመጨረሻ ጻድቃን እንሆናለን፡፡ በእውነት ጻድቃን የሆኑ ሰዎች በኢየሱስ ጥምቀትና ደም ወንጌል እምነት ዳግም የተወለዱ ሰዎች ናቸው፡፡
- Prima
1-32. Poiché Dio è grazioso e compassionevole, non ci considererebbe giusti, anche se nel nostro cuore c’è peccato, se crediamo semplicemente in Gesù?
- Dopo
1-33. Se diciamo che Gesù ha già eliminato tutti i nostri peccati del passato, del presente e del futuro secondo la tua affermazione, come si svilupperebbe il futuro di una persona se continuasse a peccare, pensando al fatto che ha già ottenuto il perdono dei suoi peccati credendo nel battesimo di Gesù e nella Croce? Anche se questa persona uccidesse un’altra persona, penserebbe che anche questo tipo di peccato gli sia stato espiato attraverso Gesù. Pertanto, continuerà a peccare senza esitazione, credendo semplicemente che Gesù abbia già eliminato anche i peccati che commetterà in futuro. Per favore, spiegami queste cose.