Soggetto 1: Rinasce d'acqua e di Spirito
1-8. ሐጢያቶቻችንን መናዘዝ እንዲጠፉ ሊያደርጋቸው ይችላልን?
አይችልም፡፡ ሐጢያቶች በኑዛዜ አይወገዱም፡፡ የሚወገዱት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እምነት ነው፡፡ ከሐጢያቶቻችን ባነጻን በኢየሱስ ጥምቀትና ደም ስናምን ብቻ ነው፡፡ በዮርዳኖስ በጥምቀቱ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ያነጻው የኢየሱስ መንፈሳዊ ደህንነት ወንጌል ይህ ነው፡፡
የሐጢያቶች ኑዛዜ አንድ ሰው የእግዚአብሄርን ሕግ የሚያውቅበት ብቸኛው መረጃ ነው፡፡ ነገር ግን ቤዛነት ሊሰጠን የሚችለው በኢየሱስ ጥምቀትና መስቀል ስናምን ብቻ ነው፡፡
እርሱ የተጠመቀበት ውሃና የኢየሱስ ደም ሰዎችን ሁሉ ከሐጢያት ያዳነ የሰማይ እውነት ነው፡፡ ደህንነታችን የተመሰረተው ኢየሱስ የሰዎችን ሁሉ ሐጢያት እንደወሰደ በማመን ላይ እንጂ በሐጢያቶች ኑዛዜ ላይ አይደለም፡፡ የኢየሱስ ስቅለት ከእኛ ከሐጢያተኞች ለወሰዳቸው ለእነዚያ ሐጢያቶች በሙሉ የተቀበለው ቅጣት ነው፡፡
ስለዚህ እውነተኛው ደህንነታችን ያለው በዮርዳኖስ በሆነው ጥምቀትና በመስቀል ላይ በፈሰሰው ደም ላይ ነው፡፡ እኛ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ የነጻነው ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ባነጻው በኢየሱስ በማመናችን ነው፡፡
ሐጢያቶቻችንን በመናዘዝ መዳን እንደምንችል የሚሰብኩ ሰዎች የእግዚአብሄርን ደህንነት የማያውቁ ሰዎች ናቸው፡፡
ስለዚህ የእግዚአብሄር ደህንነት በሆነው የኢየሱስ ጥምቀትና ደም ማመን አለብን፡፡ መቼም ቢሆን የሰው ዘር ሐጢያቶች እነርሱን ለእግዚአብሄር በመናዘዝ ይቅር ሊባሉ ይችላሉ አትበሉ፡፡
ሐጢያቶቻችን ሲዖል እንዳስቀመጡን እወቁ፡፡ ነገር ግን ባዳነንና በእግዚአብሄር ፊት ጻድቃን ባደረገን በኢየሱስ በጥምቀቱና በደሙ ማመናችን ሐጢያቶቻችንን ማስወገድ ይችላል፡፡ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ መዳን የምንችልበት ብቸኛው መንገድ ይህ ነው፡፡ ሁላችንም በአንድ ጊዜ ከሐጢያቶቻችን የነጻነው የውሃውንና የደሙን የእውነት ቃሎች በማመናችን መሆኑን እንወቅ፡፡ (1ኛ ዮሐንስ 5፡4-8)
በተናዘዝን ጊዜ ሁሉ ሐጢያቶቻችንን አይደመስሱም፡፡ በኑዛዜ ላይ በመደገፍ ሙጭጭ የምትሉ ከሆነ መጨረሻችሁ ሲዖል ይሆናል፡፡ በልባችን ውስጥ ያሉት ሐጢያቶች ይነጹ ዘንድ በእውነተኛው ወንጌል እንመን፡፡ በጭንቅላታችሁ ብቻ ሳይሆን በልባችሁም እመኑ፡፡ ለዘላለምም ከሐጢያቶቻችሁ ነጻ ሁኑ፡፡
- Prima
1-32. Poiché Dio è grazioso e compassionevole, non ci considererebbe giusti, anche se nel nostro cuore c’è peccato, se crediamo semplicemente in Gesù?
- Dopo
1-33. Se diciamo che Gesù ha già eliminato tutti i nostri peccati del passato, del presente e del futuro secondo la tua affermazione, come si svilupperebbe il futuro di una persona se continuasse a peccare, pensando al fatto che ha già ottenuto il perdono dei suoi peccati credendo nel battesimo di Gesù e nella Croce? Anche se questa persona uccidesse un’altra persona, penserebbe che anche questo tipo di peccato gli sia stato espiato attraverso Gesù. Pertanto, continuerà a peccare senza esitazione, credendo semplicemente che Gesù abbia già eliminato anche i peccati che commetterà in futuro. Per favore, spiegami queste cose.