Поширені запитання щодо Християнської Віри
Запитання 1: Народження знову з води та Духа
1-15. የሐጢያት ስርየት የተሰጠው በአንዴ ነው ወይስ ቀስ በቀስ?
ይህ በአንድ ጊዜ የተሰጠ ነው፡፡ ምክንያቱም ኢየሱስ አንድ ጊዜ በመጠመቅና ፍርድንም አንድ ጊዜ በመውሰድ ሐጢያቶቻችንን ወስዶዋልና፡፡ በማቴዎስ 3፡15 ላይ እንደተመዘገበው እርሱ ‹‹አሁንስ ፍቀድልኝ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና›› ብሎዋል፡፡
በዮሐንስ 1፡29 ላይ አጥማቂው ዮሐንስ እንዲህ አለ፡- ‹‹እነሆ የዓለምን ሐጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሄር በግ፡፡›› እንዲሁም በዮሐንስ 19፡30 ላይ ኢየሱስ ‹‹ተፈጸመ!›› አለ፡፡
ዕብራውያን 10፡9-18 እንዲህ ይላል፡- ‹‹ቀጥሎ፡- እነሆ አምላኬ ሆይ ፈቃድህን ላደርግ መጥቼአለሁ ብሎአል፡፡ ሁለተኛውን ሊያቆም የፊተኛውን ይሽራል፡፡ በዚህም ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ በማቅረብ አንድ ጊዜ ተቀድሰናል፡፡ ሊቀ ካህናትም ሁሉ ዕለት ዕለት እያገለገለ ሐጢአትን ከቶ የማይችሉትን እነዚያን መስዋዕቶች ብዙ ጊዜ እያቀረበ ቆሞአል፡፡ እርሱ ግን ስለ ሐጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘለዓለም አቅርቦ በእግዚአብሄር ቀኝ ተቀመጠ፡፡ ጠላቶቹም የእግሩ መረገጫ እስኪደረጉ ድረስ ወደፊት ይጠብቃል፡፡ አንድ ጊዜ በማቅረብ የሚቀደሱትን የዘላለም ፍጹማን አድርጎአቸዋልና፡፡ መንፈስ ቅዱስም ደግሞ ስለዚህ ይመሰክርልናል፡፡ ከዚያ ወራት በኋላ ከእነርሱ ጋር የምገባው ኪዳን ይህ ነው ይላል ጌታ፤ በልባቸው ሕጌን አኖራለሁ፤ በልቡናቸውም እጽፈዋለሁ ብሎ ከተናገረ በኋላ ሐጢአታቸውንና ዓመጻቸውንም ደግሜ አላስብም ይላል፡፡ የእነዚህም ስርየት ባለበት ዘንድ ከእንግዲህ ወዲያ ስለ ሐጢአት ማቅረብ የለም፡፡›› የኢየሱስ ጥምቀትና ደም የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ለዘላለም ደምስሶዋል፡፡
- До
1-32.: Якщо, як ви кажете, Ісус вже взяв на себе всі гріхи, минулі, теперішні і майбутні, то що станеться з майбутнім людини, якщо вона продовжуватиме грішити, думаючи, що її гріхи були змиті хрещенням і вірою в Ісуса на хресті? Навіть якщо ця людина вб’є іншу людину, вона буде думати, що навіть цей гріх вона вже спокутувала через Ісуса. Тому він продовжуватиме грішити без будь-яких вагань, просто вірячи, що Ісус уже усунув навіть ті гріхи, які він зробить у майбутньому. Поясніть мені, будь ласка, про ці речі.