• 所有新生命宣教会 The New Life Mission 网站上的电子书和有声书均可免费下载
  • 探索以多种语言提供的全球性讲道
  • 查看我们已翻译成27种语言的网站
  • 第1卷新修订版已全新推出
Search

关于基督教信仰的常见问题解答

话题1:重生于水和圣灵

1-15. የሐጢያት ስርየት የተሰጠው በአንዴ ነው ወይስ ቀስ በቀስ? 

ይህ በአንድ ጊዜ የተሰጠ ነው፡፡ ምክንያቱም ኢየሱስ አንድ ጊዜ በመጠመቅና ፍርድንም አንድ ጊዜ በመውሰድ ሐጢያቶቻችንን ወስዶዋልና፡፡ በማቴዎስ 3፡15 ላይ እንደተመዘገበው እርሱ ‹‹አሁንስ ፍቀድልኝ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና›› ብሎዋል፡፡ 
በዮሐንስ 1፡29 ላይ አጥማቂው ዮሐንስ እንዲህ አለ፡- ‹‹እነሆ የዓለምን ሐጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሄር በግ፡፡›› እንዲሁም በዮሐንስ 19፡30 ላይ ኢየሱስ ‹‹ተፈጸመ!›› አለ፡፡ 
ዕብራውያን 10፡9-18 እንዲህ ይላል፡- ‹‹ቀጥሎ፡- እነሆ አምላኬ ሆይ ፈቃድህን ላደርግ መጥቼአለሁ ብሎአል፡፡ ሁለተኛውን ሊያቆም የፊተኛውን ይሽራል፡፡ በዚህም ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ በማቅረብ አንድ ጊዜ ተቀድሰናል፡፡ ሊቀ ካህናትም ሁሉ ዕለት ዕለት እያገለገለ ሐጢአትን ከቶ የማይችሉትን እነዚያን መስዋዕቶች ብዙ ጊዜ እያቀረበ ቆሞአል፡፡ እርሱ ግን ስለ ሐጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘለዓለም አቅርቦ በእግዚአብሄር ቀኝ ተቀመጠ፡፡ ጠላቶቹም የእግሩ መረገጫ እስኪደረጉ ድረስ ወደፊት ይጠብቃል፡፡ አንድ ጊዜ በማቅረብ የሚቀደሱትን የዘላለም ፍጹማን አድርጎአቸዋልና፡፡ መንፈስ ቅዱስም ደግሞ ስለዚህ ይመሰክርልናል፡፡ ከዚያ ወራት በኋላ ከእነርሱ ጋር የምገባው ኪዳን ይህ ነው ይላል ጌታ፤ በልባቸው ሕጌን አኖራለሁ፤ በልቡናቸውም እጽፈዋለሁ ብሎ ከተናገረ በኋላ ሐጢአታቸውንና ዓመጻቸውንም ደግሜ አላስብም ይላል፡፡ የእነዚህም ስርየት ባለበት ዘንድ ከእንግዲህ ወዲያ ስለ ሐጢአት ማቅረብ የለም፡፡›› የኢየሱስ ጥምቀትና ደም የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ለዘላለም ደምስሶዋል፡፡ 
The New Life Mission

参加我们的调查

您是如何了解到我们的?