• 所有新生命宣教会 The New Life Mission 网站上的电子书和有声书均可免费下载
  • 探索以多种语言提供的全球性讲道
  • 查看我们已翻译成27种语言的网站
  • 第1卷新修订版已全新推出
Search

关于基督教信仰的常见问题解答

话题1:重生于水和圣灵

1-17. ኢየሱስ በመስቀል ላይ የሞተው ለምንድነው? 

የኢየሱስ ሞት በጥምቀቱ አማካይነት ለተወሰዱ ሐጢያቶች በሙሉ የተከፈለ ክፍያ ነበር፡፡ ሰዎች ለሐጢያቶቻቸው ዘላለማዊ የሲዖል እሳት ተጋፍጦዋቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ኢየሱስ ስለወደደን ሐጢያቶቻችን በሙሉ ወደ ራሱ የተላለፉበትን ጥምቀት ተቀብሎ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ ሞተ፡፡ 
እርሱ እኛን ከሐጢያትና ከሲዖል እርግማን ለማዳን ራሱን መስዋዕት አደረገ፡፡ የእርሱ ሞት ለሰው ዘር ሐጢያቶች የተከፈለ ክፍያ ነበር፡፡ እርሱ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ለመውሰድ ተጠመቀ፡፡ ሁላችንንም ከሐጢያት ከሞት ከፍርድና ከኩነኔ ለማዳንም በመስቀል ላይ ራሱን ለፍርድ ሰጠ፡፡    
ኢየሱስ የሞተው ለሰው ዘር ሐጢያቶች ፍርድን ይቀበል ዘንድ በዮርዳኖስ በራሱ ላይ ለወሰዳቸው የዓለም ሐጢያቶች ነበር፡፡ እርሱ በመስቀል ላይ ሞተ፡፡ ዳግመኛ ጻደቃን ሆነን እንድንኖር ሊፈቅድልን ከሙታን ተነሳ፡፡   
The New Life Mission

参加我们的调查

您是如何了解到我们的?