• 所有新生命宣教会 The New Life Mission 网站上的电子书和有声书均可免费下载
  • 探索以多种语言提供的全球性讲道
  • 查看我们已翻译成27种语言的网站
  • 第1卷新修订版已全新推出
Search

关于基督教信仰的常见问题解答

话题2:圣灵

2-7. የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉት በሐጢያት ይቅርታ አማካይነት ከሐጢያቶቻቸው ስለዳኑ ነው ወይስ ይህ የሐጢያት ይቅርታን በማይመለከት ሁኔታ የተነጠለ ልምምድ ነበር? 

መንፈስ ቅዱስ ከቤዛነት የተነጠለ ልምምድ አይደለም፡፡ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት መንፈስ ቅዱስን ከመቀበላቸው በፊት እንኳን ኢየሱስ በዮሐንስ ጥምቀት አማካይነት የአለምን ሐጢያቶች በሙሉ መውሰዱን ቀደሞውኑም አውቀውና አምነው እንደነበር በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ማየት እንችላለን፡፡ (1ኛ ጴጥሮስ 3፡21 ‹‹ጥምቀት ምሳሌው ሆኖ አሁን ያድነናል፡፡››) 
የሐጢያት ይቅርታ ማለት ከሐጢያት መዳን ማለት ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ይህ ማለት በልቦቻችን ውስጥ ያሉት ሐጢያቶች በሙሉ ነጽተው ተወግደዋል ማለት ነው፡፡ ዛሬ ብዙ ክርስቲያኖች ኢየሱስ ስለሰጠን የሐጢያት ይቅርታ ትርጉም አብዛኛውን ጊዜ ግራ ይጋባሉ፡፡ ሰዎች እንዴት የሐጢያት ይቅርታን መቀበል እንደሚችሉ አያውቁም፡፡ ኢየሱስን ጌታቸው አድርገው ስለሚያምኑ ብቻ እንደዳኑ ያስባሉ፡፡
የሐጢያቶቻቸውን ይቅርታ የተቀበሉ ሰዎች በራሳቸው ውስጥ ምስክር አላቸው፡፡ ሆኖም አንድ ሰው የቤዛነቱ ምስክር ቃል ከሌለው መንፈስ ቅዱስን አልተቀበለም፤ ከሐጢያቶቹም ሁሉ ይቅርታን አላገኘም፡፡ በመንፈስ የተሞሉ ስሜቶች ካሉትም ያ በገዛ ራሱ ስሜቶች እየተታለለ የመሆኑ ውጤት ብቻ ነው፡፡ ሰይጣን ራሱን ወደ ብርሃን መልአክ ይለውጥና (2ኛ ቆሮንቶስ 11፡14-15፤ ገላትያ 1፡7-9) ከእውነት እንዲርቅ ያታልለዋል፡፡ (ማቴዎስ 7፡21-23) 
የሐጢያቶቻቸውን ስርየት ያገኙ ሰዎች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ስለሚያምኑ በውስጣቸው ምስክር አላቸው፡፡ በ1ኛ ዮሐንስ 5፡4-12 ላይ በውሃና በደም ለመጣው ኢየሱስ ክርስቶስ ይመሰክራል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም አንድ ሰው ስለ ልዩ መንፈስ ወይም ልዩ ወንጌል የሚሰብክ ከሆነ (2ኛ ቆሮንቶስ 11፡4) እርሱ የሐጢያት ስርየትንም ሆነ መንፈስ ቅዱስን እንዳልተቀበለ ይናገራል፡፡ ሰዎች የሐጢያት ይቅርታን መቀበል የሚችሉት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በመጣው በኢየሱስ ክርስቶስ በሚያምኑበት ጊዜ ብቻ ነው፡፡ የሐጢያት ይቅርታ ዘለቄታዊውን መንፈስ ቅዱስ ለመቀበል ወሳኝ ነው፡፡ 
The New Life Mission

参加我们的调查

您是如何了解到我们的?