• 所有新生命宣教会 The New Life Mission 网站上的电子书和有声书均可免费下载
  • 探索以多种语言提供的全球性讲道
  • 查看我们已翻译成27种语言的网站
  • 第1卷新修订版已全新推出
Search

关于基督教信仰的常见问题解答

话题4:读者的经常提问及解答

4-2. ‹‹በልባችን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ስናምን ፈጽሞ ሐጢያት አልባ መሆን እንችላለን›› ብለህ ጻፍህ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ግን እንዲህ ይላል፡- ሐጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን፤ እውነትም በእኛ ውስጥ የለም፡፡ በሐጢአታችን ብንናዘዝ ሐጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመጻም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው፡፡ ሐጢአት አላደረግንም ብንል ሐሰተኛ እናደርገዋለን፤ ቃሉም በእኛ ውስጥ የለም፡፡›› (1ኛ ዮሐንስ 1፡8-10) ይህንን ምንባብ እንዴት ትተረጉመዋለህ? ምንባቡ የሚለው እኛ እስከ ምንሞት ድረስ ሐጢያተኞች እንደሆንንና በየቀኑም የሐጢያቶቻችንን ይቅርታ ለማግኘት የንስሐ ጸሎቶችን ማቅረብ እንዳለብን አይደለምን?

1ኛ ዮሐንስ 1፡8-10 እንዲህ ይላል፡- ‹‹ሐጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን፤ እውነትም በእኛ ውስጥ የለም፡፡ በሐጢአታችን ብንናዘዝ ሐጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመጻም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው፡፡ ሐጢአት አላደረግንም ብንል ሐሰተኛ እናደርገዋለን፤ ቃሉም በእኛ ውስጥ የለም፡፡››  
‹‹ሐጢአት የለብንም ብንል›› ማለት ‹‹ሐጢያተኛ ሆነን እንደተወለድን ካልተናዘዝንና በሕጉ ፊትም በሕይወት ዘመናችን በሙሉ ሐጢያት እየሰራን የምንቀጥል ከሆነ›› ማለት ነው፡፡ እንደምናውቀው ሁሉም ሰው ሐጢያቱን መናዘዝ አለበት፡፡ ሆኖም ይህ ማለት ለእነዚያ ሐጢያቶች በየቀኑ ይቅርታን ለማግኘት የዘወትር ሐጢያቶቻችንን መናዘዝ አለብን ማለት ሳይሆን በኢየሱስ ሳናምን በራሳችን ሐጢያት መስራትን ለመሸሽ በጣም ደካሞች መሆናችንን መናዘዝ ይገባናል ማለት ነው፡፡ ስለዚህ አንድ ሰው በልቡ ውስጥ ሐጢያት ይዞ በጨለማ ውስጥ እየኖረ ሐጢያት እንደሌለበት የሚናገር ከሆነ በእርሱ ውስጥ እውነት የለም፡፡
     
‹‹ሐጢአታችንን ብንናዘዝ›› ማለት ‹‹ከውልደታችን ጊዜ ጀምሮ እስከምንሞትበት ቀን ድረሰ ሁሌም ሐጢያት እንደምንሰራና ሐጢያት መስራትን መሸሽ ብንፈልግም እንኳን ሐጢያት ሳንሰራ መኖር እንደማንችል መናዘዝ ነው፡፡›› ሐጢያት በምንሰራበት ጊዜ ሁሉ ንስሐ መግባትና የጌታን ይቅርታ መጠየቅ ማለት አይደለም፡፡ ጌታ ከ2,000 ዓመት በፊት በጥምቀቱና በመስቀሉ ቀድሞውኑም የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ደምስሶዋል፡፡ አሁን እኛ ማድረግ ያለብን ነገር ቢኖር እኛ ያለ እርሱ ሐጢያተኞች እንደሆንንና የእርሱ ወንጌል ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለአንዴና ለመጨረሻ እንደደመሰሰ መናዘዝ ነው፡፡
  
‹‹ሐጢአት አላደረግንም ብንል ሐሰተኛ እናደርገዋለን፤ ቃሉም በእኛ ውስጥ የለም›› ማለት የሚከተለውን ነው፡፡ ሕጉ የሐጢያትን ዕውቀት ይሰጠንና በልቦቻችን ውስጥ የተደበቁትን ሐጢያቶች ይገልጣል፡፡ ስለዚህ በሕጉ ፊት ሐጢያት መስራታችንን መናዘዝ ይኖርብናል፡፡ ሆኖም ሕጉን የማይቀበሉ ሰዎች ሐጢያት እንደሰሩ አይናዘዙም፡፡ ሕጉ ሐጢያቶቻችንን እንድንናዘዝ ያደርገንና በጥምቀቱና በመስቀሉ አማካይነት የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ወዳነጻው ኢየሱስ ይመራናል፡፡
The New Life Mission

参加我们的调查

您是如何了解到我们的?