• 所有新生命宣教会 The New Life Mission 网站上的电子书和有声书均可免费下载
  • 探索以多种语言提供的全球性讲道
  • 查看我们已翻译成27种语言的网站
  • 第1卷新修订版已全新推出
Search

关于基督教信仰的常见问题解答

话题4:读者的经常提问及解答

4-10. ‹‹የእውነትን እውነት ከተቀበልን በኋላ ወደን ሐጢአትን ብናደርግ›› (ዕብራውያን 10፡26) ማለት ምን ማለት ነው?

የጠቀስከው ምንባብ ትርጓሜ ይኸውልህ፡፡
‹‹የእውነትን እውቀት ከተቀበልን በኋላ ወደን ሐጢአት ብናደርግ ከእንግዲህ ወዲህ ስለ ሐጢአት መሥዋዕት አይቀርልንምና፡፡ የሚያስፈራ ግን የፍርድ መጠበቅ ተቃዋሚዎችንም ሊበላ ያለው የእሳት ብርታት አለ፡፡››     
አሁን በእውነት እውቀት ማለትም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ እምነት ሊኖርህ ይችላል፡፡ 
ታዲያ ‹‹ወዶ ሐጢያት ማድረግ›› ምን ማለት ነው? 
ሐጢያት በሁለት መደቦች ሊከፈል እንደሚችል ማወቅ አለብን፡፡ ‹‹ሞት የሚገባው ሐጢያት›› እና ‹‹ሞት የማይገባው ሐጢያት፡፡›› (1ኛ ዮሐንስ 5፡16)   
ነገር ግን ‹‹ሞት የሚገባው ሐጢያት›› መንፈስ ቅዱስን የመሳደብ ሐጢያት ነው፡፡ 
‹‹ስለዚህ እላችኋለሁ፤ ሐጢአትና ስድብ ሁሉ ለሰዎች ይሰረይላቸዋል፤ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስን ለሰደበ አይሰረይለትም፡፡›› (ማቴዎስ 12፡31) መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስ እውነተኛ አዳኝ እንደሆነ ይመሰክራል፤ ዳግመኛ በተወለዱ ቅዱሳኖች አማካይነትም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ይመሰክራል፡፡ 
በአጭሩ ሰው መላውን ይዘቶቹን ከሰማ በኋላ እውነተኛውን ወንጌል የሚክድ ከሆነ ያን ጊዜ ይህ ሰው መንፈስ ቅዱስን የሚሳደብ ሐጢያት እየሰራ ነው፡፡ የሚያሳዝነው በወንጌል ምክንያት አንዳንድ ችግሮች በሚገጥሙዋቸው ጊዜ ወንጌልን የሚክዱ ሰዎች ያሉ መሆናቸው ነው፡፡
ሰው እውነት መሆኑን እያወቀ እውነተኛውን ወንጌል በውዴታ የሚክድ ከሆነ እግዚአብሄር የዚህን ሰው እንዲህ ያለ ሐጢያት ይቅር ሊለው ይችላልን? እግዚአብሄር እንዲህ ባለ ሐጢያት ላይ በግልጥ ዘላለማዊ ኩነኔን ያውጃል፡፡
The New Life Mission

参加我们的调查

您是如何了解到我们的?