• 所有新生命宣教会 The New Life Mission 网站上的电子书和有声书均可免费下载
  • 探索以多种语言提供的全球性讲道
  • 查看我们已翻译成27种语言的网站
  • 第1卷新修订版已全新推出
Search

会幕研究

ቅድስተ ቅዱሳን

ቅድስተ ቅዱሳን
 
ቅድስተ ቅዱሳኑ እግዚአብሄር የሚያድርበት ስፍራ ነው፡፡ በቅድሰተ ቅዱሳኑ ውስጥ ክንፎቻቸውን የዘረጉ ሁለት ኪሩቤሎች ከላይ ሆነው የምስክሩን ታቦት የሸፈነውን ክዳን ተመለከቱ፡፡ በሁለቱ ኪሩቤሎች መካከል ያለ ባዶ ስፍራ የምህረት መቀመጫ ተብሎ ይጠራል፡፡ የምህረት መቀመጫው እግዚአብሄር ጸጋውን ለእኛ የለገሰበት ነው፡፡ የምስክሩ ታቦት መሸፈኛ ሊቀ ካህኑ ለእስራኤል ሕዝብ የተሰጠውን የመሰዋዕቱን ደም በምህረት መቀመጫው ላይ ሰባት ጊዜ ስለረጨው በደም ተበክሎ ነበር፡፡  
ለእስራኤላውያን ሐጢያቶች ስርየት ለመስዋዕት የቀረበውን ፍየል ደም ይዞ በዓመት አንድ ጊዜ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን መግባት የሚችለው ሊቀ ካህኑ ብቻ ነው፡፡ ይህንን ያደረገው የመገናኛው ድንኳን ቅድስተ ቅዱሳን የሆነው የእግዚአብሄር ቤት የሐጢያተኞችን ሐጢያቶች ለመደምሰስ እጆቹን በራሱ ላይ ጭኖ የመስዋዕቱን ደም ካልያዘ በስተቀር ሊገባበት የማይችልበት ቅዱስ ስፍራ ነበርና፡፡ 
እግዚአብሄር እንዲህ በምህረት መቀመጫው ላይ ወረደና ምህረቱን ለእስራኤል ሕዝብ ለገሰ፡፡ በዚህ ለሚያምኑ ሰዎች የእግዚአብሄር በረከቶች፣ ጥበቃና ምሪት ይጀምራል፡፡ ከዚያ ጀምሮ እነርሱ የእግዚአብሄር እውነተኛ ሕዝብ ይሆኑና ወደ ቅድስቱ ስፍራ ለመግባት ብቁ ይሆናሉ፡፡

下载相关推荐书籍

The New Life Mission

参加我们的调查

您是如何了解到我们的?