Fragen und Antworten zum christlichen Glauben
Thema 1: Die Wiedergeburt aus Wasser und Geist
1-6. የንስሐ ጸሎቶች ሐጢያቶቻችንን ማስወገድ ይችላሉን?
ቤዛነት ፈጽሞ በሥራዎቻችን አማካይነት ስለማይመጣ የንስሐ ጸሎቶችም ሐጢያቶቻችንን በፍጹም ማንጻት አይችሉም፡ ሐጢያቶቻችን ፈጽሞ ለዘለቄታው ይነጹ ዘንድ በኢየሱስ ጥምቀትና ደም እንደዚሁም ኢየሱስ አምላክ እንደሆነ ማመን ይኖርብናል፡፡ እውነተኛ ቤዛነት የሚሰጠው ኢየሱስ አዲስ ሕይወትን ይሰጠን ዘንድ በጥምቀቱና በመስቀል ላይ ደሙን በማፍሰሱ ሐጢያቶቻችንን እንዳነጻ ለሚያምኑ ሰዎች ነው፡፡
የንስሐ ጸሎቶችን በማቅረብ በየቀኑ የምንሰራቸውን ሐጢያቶች ማንጻት እንችላለን? አንችልም፡፡ በሕይወታችን የሰራናቸው ሐጢያቶች በሙሉ ኢየሱስ በጥምቀቱ በወሰዳቸው ጊዜ ቀድሞውኑም ከ2,000 ዓመታት በፊት ነጽተዋል፡፡ እኛም በኢየሱስ ጥምቀትና በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደሙ ለዘላለም ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ነጽተናል፡፡ እርሱ ለእኛ ለምዕመናን የመስዋዕት በግ ሆነ፡፡ ሐጢያቶቻችንንም በሙሉ አስወገደ፡፡ በጥምቀቱና በመስቀል ላይ ደሙም የሁሉንም ዋጋ ከፈለ፡፡
በኢየሱስ ካመንን በኋላ የምንሰራቸው ሐጢያቶችም እንኳን የቤዛነት እውነት በሆነው የጥምቀቱ ደህንነት ምንጭ እምነት ተወግዶዋል፡፡ ኢየሱስ ቀድሞውኑም አዳኛችን ሆኖ እስከ ዕለተ ሞታችን ድረስ የምንሰራቸውን ሐጢያቶች በሙሉ ወስዶዋል፡፡ ኢየሱስ ወደዚህ ዓለም መጥቶ ‹‹እንዲህ›› (ማቴዎስ 3፡15) በመጠመቅ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ወስዶ ጽድቅን ሁሉ ፈጸመ፡፡ የእግዚአብሄር ልጅ በጥምቀቱ የሐጢያቶቻችንን ሐላፊነት ወሰደ፡፡
የኢየሱስ ጥምቀት ‹‹መታጠብ›› የሚል ትርጉም አለው፡፡ ኢየሱስ በተጠመቀ ጊዜ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ወደ እርሱ ስለተላለፉ እኛ ፈጽሞ ከሐጢያቶቻችንን ሁሉ ነጻ አውጥቶናል፡፡
ጥምቀት ማለት ‹‹መጥለም፣ መቀበር›› ማለትም ነው፡፡ ሐጢያቶቻችን በሙሉ ወደ ኢየሱስ ስለተላለፉ እርሱ ለእኛ ለሐጢያተኞች መሞት ነበረበት፡፡ ሐጢያቶች በሙሉ በእርሱ ጥምቀት አማካይነት ወደ ኢየሱስ እንደተላለፉ የሚያምኑ ሰዎች ለዘላለም ሐጢያት አልባ ሆነዋል፡፡
እውነተኛ እምነት ሐጢያቶቻችን በሙሉ፤ አሁንና ወደፊት የምንሰራውም ሐጢያቶች እንኳን ኢየሱስ ጥምቀትን ከዮሐንስ በተቀበለና ‹‹እንዲህ›› የእግዚአብሄርን ጽድቅ ሁሉ በፈጸመ ጊዜ ከ2,000 ዓመታት በፊት ወደ ኢየሱስ እንደተላለፉ በሙሉ ልብ ማመን ነው፡፡
እርሱ ቀድሞውኑም በጥምቀቱ ሐጢያቶቻችንን ከረጅም ጊዜ በፊት ባያስወግድ ኖሮ አሁን እኛ ከሐጢያቶቻችን የምንነጻበት መንገድ አይኖረንም ነበር፡፡ ኢየሱስ ከረጅም ጊዜ በፊት ሐጢያቶቻችንን በሙሉ እንዳስወገደ አስታውሱ፡፡
ዛሬ እውነተኛ እምነትና መንፈሳዊ ደህንነት ማለት ‹‹እነዚህን ሐጢያቶችም ደግሞ አስወግደሃል አይደል?›› በማለት ቀድሞውኑም መንጻታቸውን ለማረጋገጥ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ በኢየሱስ ፊት ማቅረብ ማለት ነው፡ ይህ ማለት እርሱን ማመንና ማመስገንም ማለት ነው፡፡ ወደ ምድር የመጣው፣ የተጠመቀው፣ በመስቀል ላይ የሞተው፣ ከዚያም በሦስተኛው ቀን የተነሳውና በዚህም አዳኛችን የሆነው ለዚህ ነው፡፡
ሐጢያቶቻችንን ባነጻው የኢየሱስ ጥምቀት በማመን ሐጢያቶቻቸውን ያስወገዱ ሰዎች የተባረኩ ናቸው፡፡ ይህ በየቀኑ ከምንሰራቸው ሐጢያቶች የመንጻት እውነት ነው፡፡ እውነተኛ እምነት በጥምቀቱ አማካይነት የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ በወሰደው በኢየሱስ ማመን ነው፡፡
- Vor
1-32. Wenn wir sagen, dass Jesus bereits alle unsere Sünden der Vergangenheit, der Gegenwart und der Zukunft gemäß Ihrer Behauptung beseitigt hat, wie würde sich dann die Zukunft einer Person gestalten, wenn sie ständig Sünden begeht, indem sie daran denkt, dass ihr ihre Sünden bereits durch den Glauben an die Taufe und das Kreuz Jesu vergeben wurden? Selbst wenn dieser Mensch einen anderen Menschen tötet, wird er denken, dass er selbst für diese Art von Sünde durch Jesus am Kreuz gesühnt worden ist. Daher wird er weiterhin ohne zu zögern sündigen, indem er einfach glaubt, dass Jesus bereits auch die Sünden beseitigt hat, die er in der Zukunft begehen wird. Bitte erklären Sie mir diese Dinge.