Fragen und Antworten zum christlichen Glauben
Thema 1: Die Wiedergeburt aus Wasser und Geist
1-8. ሐጢያቶቻችንን መናዘዝ እንዲጠፉ ሊያደርጋቸው ይችላልን?
አይችልም፡፡ ሐጢያቶች በኑዛዜ አይወገዱም፡፡ የሚወገዱት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እምነት ነው፡፡ ከሐጢያቶቻችን ባነጻን በኢየሱስ ጥምቀትና ደም ስናምን ብቻ ነው፡፡ በዮርዳኖስ በጥምቀቱ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ያነጻው የኢየሱስ መንፈሳዊ ደህንነት ወንጌል ይህ ነው፡፡
የሐጢያቶች ኑዛዜ አንድ ሰው የእግዚአብሄርን ሕግ የሚያውቅበት ብቸኛው መረጃ ነው፡፡ ነገር ግን ቤዛነት ሊሰጠን የሚችለው በኢየሱስ ጥምቀትና መስቀል ስናምን ብቻ ነው፡፡
እርሱ የተጠመቀበት ውሃና የኢየሱስ ደም ሰዎችን ሁሉ ከሐጢያት ያዳነ የሰማይ እውነት ነው፡፡ ደህንነታችን የተመሰረተው ኢየሱስ የሰዎችን ሁሉ ሐጢያት እንደወሰደ በማመን ላይ እንጂ በሐጢያቶች ኑዛዜ ላይ አይደለም፡፡ የኢየሱስ ስቅለት ከእኛ ከሐጢያተኞች ለወሰዳቸው ለእነዚያ ሐጢያቶች በሙሉ የተቀበለው ቅጣት ነው፡፡
ስለዚህ እውነተኛው ደህንነታችን ያለው በዮርዳኖስ በሆነው ጥምቀትና በመስቀል ላይ በፈሰሰው ደም ላይ ነው፡፡ እኛ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ የነጻነው ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ባነጻው በኢየሱስ በማመናችን ነው፡፡
ሐጢያቶቻችንን በመናዘዝ መዳን እንደምንችል የሚሰብኩ ሰዎች የእግዚአብሄርን ደህንነት የማያውቁ ሰዎች ናቸው፡፡
ስለዚህ የእግዚአብሄር ደህንነት በሆነው የኢየሱስ ጥምቀትና ደም ማመን አለብን፡፡ መቼም ቢሆን የሰው ዘር ሐጢያቶች እነርሱን ለእግዚአብሄር በመናዘዝ ይቅር ሊባሉ ይችላሉ አትበሉ፡፡
ሐጢያቶቻችን ሲዖል እንዳስቀመጡን እወቁ፡፡ ነገር ግን ባዳነንና በእግዚአብሄር ፊት ጻድቃን ባደረገን በኢየሱስ በጥምቀቱና በደሙ ማመናችን ሐጢያቶቻችንን ማስወገድ ይችላል፡፡ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ መዳን የምንችልበት ብቸኛው መንገድ ይህ ነው፡፡ ሁላችንም በአንድ ጊዜ ከሐጢያቶቻችን የነጻነው የውሃውንና የደሙን የእውነት ቃሎች በማመናችን መሆኑን እንወቅ፡፡ (1ኛ ዮሐንስ 5፡4-8)
በተናዘዝን ጊዜ ሁሉ ሐጢያቶቻችንን አይደመስሱም፡፡ በኑዛዜ ላይ በመደገፍ ሙጭጭ የምትሉ ከሆነ መጨረሻችሁ ሲዖል ይሆናል፡፡ በልባችን ውስጥ ያሉት ሐጢያቶች ይነጹ ዘንድ በእውነተኛው ወንጌል እንመን፡፡ በጭንቅላታችሁ ብቻ ሳይሆን በልባችሁም እመኑ፡፡ ለዘላለምም ከሐጢያቶቻችሁ ነጻ ሁኑ፡፡
- Vor
1-32. Wenn wir sagen, dass Jesus bereits alle unsere Sünden der Vergangenheit, der Gegenwart und der Zukunft gemäß Ihrer Behauptung beseitigt hat, wie würde sich dann die Zukunft einer Person gestalten, wenn sie ständig Sünden begeht, indem sie daran denkt, dass ihr ihre Sünden bereits durch den Glauben an die Taufe und das Kreuz Jesu vergeben wurden? Selbst wenn dieser Mensch einen anderen Menschen tötet, wird er denken, dass er selbst für diese Art von Sünde durch Jesus am Kreuz gesühnt worden ist. Daher wird er weiterhin ohne zu zögern sündigen, indem er einfach glaubt, dass Jesus bereits auch die Sünden beseitigt hat, die er in der Zukunft begehen wird. Bitte erklären Sie mir diese Dinge.