Fragen und Antworten zum christlichen Glauben
Thema 2: Der Heilige Geist
2-9. መንፈስ ቅዱስ በብሉይና በአዲስ ኪዳናት ውስጥ እንዴት የተለያየ ሆኖ ይገለጣል?
መንፈስ ቅዱስ ጊዜው ምንም ይሑን ያው እግዚአብሄር ነው፡፡ ስለዚህ ስለ እርሱ በብሉይ ወይም በአዲስ ኪዳን ውስጥ ብናነብ መለኮታዊ ባህርይው አይለወጥም፡፡ ሆኖም በእግዚአብሄር ችሮታ የሰውን ዘር ከሐጢያቶቻቸው ለማዳን በብሉይና በአዲስ ኪዳናት ውስጥ በተለየ ሁኔታ መስራቱ እውነት ነው፡፡
በብሉይ ኪዳን እግዚአብሄር ቃሎቹን እንዲናገሩ፣ ፈቀዱን በድንቆች አማካይነት እንዲያሳዩና የእርሱን ስራ እንዲሰሩ በተለዩ ዘዴዎች መንፈስ ቅዱስን በእግዚአብሄር ሰዎች ላይ አፈሰሰ፡፡ ለምሳሌ የእግዚአብሄር መንፈስ በፈራጁ ሳምሶን ላይ ወረደና በእርሱ አማካይነት ብዙ ብርቱ ሥራዎችን ሰራ፡፡ (መሳፍንት 13፡25፤14፡19) በሌላ አነጋገር በብሉይ ኪዳን መንፈስ ቅዱስ በተመረጡ ሰዎች ላይ ብቻ ወረደ፡፡
ሆኖም በአዲስ ኪዳን ዘመን እግዚአብሄር በዓለ ሃምሳን የመንፈስ ቅዱስ መምጣት የመጀመሪያ መነሻ አድርጎ በመወሰን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምን እምነታቸው አማካይነት የሐጢያቶችን ይቅርታ ላገኙ ቅዱሳን ሁሉ መንፈስ ቅዱስን ሰደደ፡፡ መንፈስ ቅዱስ በእነርሱ ውስጥ ለዘላለም እንዲኖር ፈቀደ፡፡
ስለዚህ ከኢየሱስ ትንሳኤ በኋላ ሐዋርያት በመጀመሪያው በዓለ ሃምሳ በመንፈስ ቅዱስ ከተሞሉ በኋላ በወንጌል እውነት በማመን ሐጢያቶቻቸው ይቅር የተባሉ ጻድቃን በሙሉ ዘለቄታዊው መንፈስ ቅዱስ ሊኖራቸው ይችላል፡፡ (የሐዋርያት ሥራ 2፡38) ጴጥሮስ አህዛብና ሮማዊ መቶ አለቃ ወደነበረው ወደ ቆርኔሌዎስ ቤት ገባና የኢየሱስን ጥምቀትና የመስቀል ላይ ደሙን ወንጌል ሰበከ፡፡ ጴጥሮስ ወንጌልን እየተናገረ ሳለ መንፈስ ቅዱስ ቃሉን በሰሙት ሁሉ ላይ ወረደ፡፡ (የሐዋርያት ሥራ 10፡34-45) ይህም አንድ ሰው ኢየሱስ የፈጸመውን የኢየሱስ ጥምቀትና የመስቀል ደሙን ወንጌል ሲሰማና ሲያምን በዚያው ቅጽበት መንፈስ ቅዱስን እንደ ስጦታ እንደሚቀበል ያረጋግጣል፡፡
እግዚአብሄር በእውነተኛው ወንጌል በማመን የሐጢያቶቻቸውን ሁሉ ይቅርታ ባገኙ ጻድቃን ሁሉ ውስጥ መንፈስ ቅዱስ እንዲኖር አደረገ፡፡ በብሉይ ኪዳን መንፈስ ቅዱስ ሰዎችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ የመምራትን ሚና ተጫወተ፡፡ መንፈስ ቅዱስ በአዲስ ኪዳን ለእግዚአብሄር ጽድቅ ይመሰክርና ለዚያም ዋስትና ሆኖ ይቆማል፡፡ የእግዚአብሄር ጽድቅ ማለት ኢየሱስ በጥምቀቱና በመስቀል ላይ ደሙ አማካይነት የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ይቅር አለ ማለት ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስም የደህንነት ወንጌል ዋስትና ሆኖ ይቆምና ሁሉም ሰው በዚህ እንዲያምን ያግዛል፡፡
- Vor
2-10. Ich verbrachte viele traurige Tage, nachdem mein Doktor meinen Fall als Magenkrebs diagnostizierte. Eines Tages besuchte mich ein christlicher Freund von mir und erzählte mir, dass die Teilnahme an einem Wiederauferstehungstreffen in seiner Kirche jede Krankheit heilen könne. Zu der Zeit war ich ein Atheist und es erschien mir, als sei die Macht Gottes, eine Krankheit zu heilen, zu gut um wahr zu sein. Am letzen Tag des Treffens kam jeder zum Pastor um von ihm das Handauflegen zu empfangen. Während er seine Hände auf mich legte, sagte er mir, dass ich einige unverständliche Worte wiederholen solle und fragte mich, ob ich an die heilenden Kräfte von Jesus Christus glaubte. Obwohl ich nicht wirklich von ganzen Herzen daran glaubte, war ich unglücklich und sagte ja. Und genau in dem Moment fühlte ich etwas heißes, wie Elektrizität durch mich fließen. Ich konnte meinen ganzen Körper beben fühlen und ich fühlte, dass mein Krebs geheilt war. Ich entschloss mich, auf der Stelle an den Herrn zu glauben und danach kam große Freude und Frieden in mein Herz und ich fing ein neues Leben an. Ich habe mich auch der Verbreitung des Evangeliums gewidmet. Ich denke, dass der Heilige Geist all diese Dinge bewirkt hat und ich glaube, dass Er in mir wohnt. Glauben Sie das nicht auch?