• 所有新生命宣教會 The New Life Mission 網站上的電子書和有聲書均可免費下載
  • 探索以多種語言提供的全球性講道
  • 查看我們已翻譯成27種語言的網站
  • 第1、2卷新修訂版已全新推出
Search

關於基督教信仰的常見問題解答

話題 1:重生於水和聖靈

1-15. የሐጢያት ስርየት የተሰጠው በአንዴ ነው ወይስ ቀስ በቀስ? 

ይህ በአንድ ጊዜ የተሰጠ ነው፡፡ ምክንያቱም ኢየሱስ አንድ ጊዜ በመጠመቅና ፍርድንም አንድ ጊዜ በመውሰድ ሐጢያቶቻችንን ወስዶዋልና፡፡ በማቴዎስ 3፡15 ላይ እንደተመዘገበው እርሱ ‹‹አሁንስ ፍቀድልኝ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና›› ብሎዋል፡፡ 
በዮሐንስ 1፡29 ላይ አጥማቂው ዮሐንስ እንዲህ አለ፡- ‹‹እነሆ የዓለምን ሐጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሄር በግ፡፡›› እንዲሁም በዮሐንስ 19፡30 ላይ ኢየሱስ ‹‹ተፈጸመ!›› አለ፡፡ 
ዕብራውያን 10፡9-18 እንዲህ ይላል፡- ‹‹ቀጥሎ፡- እነሆ አምላኬ ሆይ ፈቃድህን ላደርግ መጥቼአለሁ ብሎአል፡፡ ሁለተኛውን ሊያቆም የፊተኛውን ይሽራል፡፡ በዚህም ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ በማቅረብ አንድ ጊዜ ተቀድሰናል፡፡ ሊቀ ካህናትም ሁሉ ዕለት ዕለት እያገለገለ ሐጢአትን ከቶ የማይችሉትን እነዚያን መስዋዕቶች ብዙ ጊዜ እያቀረበ ቆሞአል፡፡ እርሱ ግን ስለ ሐጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘለዓለም አቅርቦ በእግዚአብሄር ቀኝ ተቀመጠ፡፡ ጠላቶቹም የእግሩ መረገጫ እስኪደረጉ ድረስ ወደፊት ይጠብቃል፡፡ አንድ ጊዜ በማቅረብ የሚቀደሱትን የዘላለም ፍጹማን አድርጎአቸዋልና፡፡ መንፈስ ቅዱስም ደግሞ ስለዚህ ይመሰክርልናል፡፡ ከዚያ ወራት በኋላ ከእነርሱ ጋር የምገባው ኪዳን ይህ ነው ይላል ጌታ፤ በልባቸው ሕጌን አኖራለሁ፤ በልቡናቸውም እጽፈዋለሁ ብሎ ከተናገረ በኋላ ሐጢአታቸውንና ዓመጻቸውንም ደግሜ አላስብም ይላል፡፡ የእነዚህም ስርየት ባለበት ዘንድ ከእንግዲህ ወዲያ ስለ ሐጢአት ማቅረብ የለም፡፡›› የኢየሱስ ጥምቀትና ደም የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ለዘላለም ደምስሶዋል፡፡ 
The New Life Mission

參加我們的調查

您是如何得知我們的?