• 所有新生命宣教會 The New Life Mission 網站上的電子書和有聲書均可免費下載
  • 探索以多種語言提供的全球性講道
  • 查看我們已翻譯成27種語言的網站
  • 第1、2卷新修訂版已全新推出
Search

關於基督教信仰的常見問題解答

話題 4:讀者的經常提問及解答

4-10. ‹‹የእውነትን እውነት ከተቀበልን በኋላ ወደን ሐጢአትን ብናደርግ›› (ዕብራውያን 10፡26) ማለት ምን ማለት ነው?

የጠቀስከው ምንባብ ትርጓሜ ይኸውልህ፡፡
‹‹የእውነትን እውቀት ከተቀበልን በኋላ ወደን ሐጢአት ብናደርግ ከእንግዲህ ወዲህ ስለ ሐጢአት መሥዋዕት አይቀርልንምና፡፡ የሚያስፈራ ግን የፍርድ መጠበቅ ተቃዋሚዎችንም ሊበላ ያለው የእሳት ብርታት አለ፡፡››     
አሁን በእውነት እውቀት ማለትም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ እምነት ሊኖርህ ይችላል፡፡ 
ታዲያ ‹‹ወዶ ሐጢያት ማድረግ›› ምን ማለት ነው? 
ሐጢያት በሁለት መደቦች ሊከፈል እንደሚችል ማወቅ አለብን፡፡ ‹‹ሞት የሚገባው ሐጢያት›› እና ‹‹ሞት የማይገባው ሐጢያት፡፡›› (1ኛ ዮሐንስ 5፡16)   
ነገር ግን ‹‹ሞት የሚገባው ሐጢያት›› መንፈስ ቅዱስን የመሳደብ ሐጢያት ነው፡፡ 
‹‹ስለዚህ እላችኋለሁ፤ ሐጢአትና ስድብ ሁሉ ለሰዎች ይሰረይላቸዋል፤ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስን ለሰደበ አይሰረይለትም፡፡›› (ማቴዎስ 12፡31) መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስ እውነተኛ አዳኝ እንደሆነ ይመሰክራል፤ ዳግመኛ በተወለዱ ቅዱሳኖች አማካይነትም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ይመሰክራል፡፡ 
በአጭሩ ሰው መላውን ይዘቶቹን ከሰማ በኋላ እውነተኛውን ወንጌል የሚክድ ከሆነ ያን ጊዜ ይህ ሰው መንፈስ ቅዱስን የሚሳደብ ሐጢያት እየሰራ ነው፡፡ የሚያሳዝነው በወንጌል ምክንያት አንዳንድ ችግሮች በሚገጥሙዋቸው ጊዜ ወንጌልን የሚክዱ ሰዎች ያሉ መሆናቸው ነው፡፡
ሰው እውነት መሆኑን እያወቀ እውነተኛውን ወንጌል በውዴታ የሚክድ ከሆነ እግዚአብሄር የዚህን ሰው እንዲህ ያለ ሐጢያት ይቅር ሊለው ይችላልን? እግዚአብሄር እንዲህ ባለ ሐጢያት ላይ በግልጥ ዘላለማዊ ኩነኔን ያውጃል፡፡
The New Life Mission

參加我們的調查

您是如何得知我們的?