Search

የእምነት መግለጫ፤

  • እኛ እናምናለን፤

    መጽሐፍ ቅዱስ ብሉይንና አዲስ ኪዳናትን ብቻ እንደያዘ፣ ቃል በቃል በመንፈስ ቅዱስ ምሪት እንደተጻፈ፣ በኦሪጅናል ማኑስክሪፕቶች ስህተት የሌለበት፣ ተዓማኒነትና ሥልጣን ያለው የእግዚአብሄር ቃል እንደሆነ፤

  • እኛ እናምናለን፤

    ለዘላለም የሚኖር አንድ ስላሴ አምላክ በሦስት ሕላዌዎች ማለትም በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ውስጥ እንደሚኖር፤

  • እኛ እናምናለን፤

    አዳም በእግዚአብሄር አምሳል ተፈጥሮ የዚህ ዓለም ገዥ በሆነው ሰይጣን ተፈትኖ እንደወደቀ እናምናለን፡፡ በአዳም ሐጢያት ምክንያት ሰዎች ሁሉ ጥፋተኝነትን ተቀብለዋል፤ በሙሉም ተበላሽተዋል፡፡ ደህንነትን ለማግኘትም በመንፈስ ቅዱስ መታደስ እንደሚያስፈልጋቸው፤

  • እኛ እናምናለን፤

    ኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሄር እንደሆነ፣ ከድንግል እንደተወለደ፣ በዮርዳኖስ ወንዝ እንደተጠመቀ፣ የእግዚአብሄር በግ ሆኖ እንደተሰቀለ፣ ዳግመኛም ከሙታን እንደተነሳና አሁን በእግዚአብሄር ቀኝ ከፍ ወዳለበት ሰማይ እንዳረገ፤

  • እኛ እናምናለን፤

    ደህንነት የሐጢያቶችን ስርየት፣ የክርስቶስን ጽድቅ መቆጠርና የዘላለምን ሕይወት እንደያዘ፤ ይህንም መቀበል የሚቻለው በስራዎች ሳይሆን በእምነት ብቻ እንደሆነ፤

  • እኛ እናምናለን፤

    የኢየሱስ ክርስቶስ ምጽዓት ቅርብ እንደሆነና የሚታይና ተጨባጭ እንደሆነ፤

  • እኛ እናምናለን፤

    የዳኑት ለዘላለም ሕይወትና በሰማይ ለሚገኘው ብርክትና እንደሚነሱና ያልዳኑት በሲዖል ለሚሆነው ዘላለማዊና ንቁ ሆነው ለሚቀበሉት ቅጣት እንደሚነሱ፤

  • እኛ እናምናለን፤

    የክርስቶስ አካል የሆነችው ቤተክርስቲያን በዳግመኛ ልደት ጊዜ ዳግመኛ የተወለዱትን፤ በክርስቶስ ውስጥም በመንፈስ ቅዱስ የተጠመቁትን ብቻ እንደምታካትት፤ እርሱ አሁን በሰማይ እንደሚማልድላቸውና ለእነርሱም ዳግመኛ እንደሚመጣላቸው፤

  • እኛ እናምናለን፤

    ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን ወደ አሕዛብ ሁሉ እንድትሄድና ወንጌልን ለእያንዳንዱ ግለሰብ እንድትሰብክ፤ የሚያምኑትንም እንድታጠምቅና እንድታስተምር እንዳዘዛት፤