Search

መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃሎች፤

አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃለ ስያሜዎች አጠር ያሉ ማብራሪያዎች

ከውሃውና ከመንፈሱ ወንጌል ጋር የተዛመዱ።

  • 1. ቤዛ

    የተጠየቀውን ዋጋ በመክፈል በምላሹ ንብረትን ወይም ግለሰብን ማስለቀቅ፤ ለዚህ መለቀቅ የተጠየቀ ወይም የተከፈለ የገንዘብ ዋጋ ወይም ክፍያ፤ ብዙውን ጊዜ መዋጀትን በአዎንታዊ መልኩ ለመግለጥ ጥቅም ላይ የዋለ (ለምሳሌ፡-ዘጸአት 21፡30 ‹ረብጣ ገንዘብ›፤ በዘሁልቁ 35፡31-32፤ በኢሳይያስ 43፡3 ላይ ‹ቤዛ›) በአዲስ ኪዳን በማቴዎስ 20፡28 እና በማርቆስ 10፡45 ላይ ቤዛን ‹‹የገንዘብ ክፍያ› አድርገው አብራርተውታል፡፡  

  • 2 . ማስተሰረይ፤ ስርየት  

    የሰዎችን ሐጢያቶች በሙሉ ወደ ኢየሱስ የማሰተላለፍ ስርዓት፡፡ በብሉይ ኪዳን ስርየት እጆችን በራሱ ላይ በመጫን ሐጢያትን ወደ መስዋዕቱ ማስተላለፍ ነበር፡፡ በአዲስ ኪዳን ስርየት ማለት በአጥማቂው ዮሐንስ የሆነው ጥምቀት ማለት ነው፡፡ በዕብራይስጥና ግሪክ ይህ ቃል ሐጢያተኞች ከእግዚአብሄር ጋር ትክክለኛ ወደሆነ ዝምድና ውስጥ ይገቡ ዘንድ ሐጢያትን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ማስተላለፍ የሚል ፍቺ አለው፡፡ አዲስ ኪዳን ለስርየት የሚቀርበውን መስዋዕት በሚገባ አብራርቶታል፡፡ ይህም የኢየሱስ ጥምቀትና በመስቀል ላይ ሞቱ ነው፡፡  
    በብሉይ ኪዳን፡- ‹ስርየት› የሚለው ቃል በብሉይ ኪዳን ውስጥ 100 ጊዜ ያህል ጥቅም ላይ ውሎዋል፡፡ ሁልጊዜም በዕብራይስጥ የተገለጠው (ዘሌዋውያን 23፡27፤25፡9፤ በዘሁልቁ 5፡8) ‹ካፋር› (ብዙውን ጊዜ የተጻፈው ‹ስርየት ማድረግ› ተብሎ ነው፡፡) ስርየት እጆችን በሕያው ፍየል ራስ ላይ በመጫንና የእስራኤሎችን በደሎች ሁሉ በእርሱ ላይ በመናዘዝ የሐጢያቶችን ማስተላለፍ የሚያመላክት የዕብራይስጥ ቃል ትርጉም ነው፡፡ (ዘሌዋውያን 16፡20)  
    ስርየት ‹ኬፕር› ከሚለው የአራማይክ ቃል ጋር ተዛምዶ ያለው ሲሆን ትርጓሜውም መሸፈን ማለት ነው፡፡ ይህም ማለት በአዲስ ኪዳን የኢየሱስ ቤዛነት ጥምቀት ማለት ነው፡፡ ኢየሱስ የሰውን ዘር ደህንነት ለመፈጸም ወደዚህ ዓለም መጥቶ በ30 ዓመቱ ተጠመቀ፡፡ 

  • 3. መጽሐፍ ቅዱሳዊው ስርየት 

    ሀ. በብሉይ ኪዳን፡- ስርየት ብዙውን ጊዜ የሚሰጠው በአንድ እንስሳ መስዋዕትነት አማካይነት ነው፡፡ (ምሳሌ፡- ዘጸአት 30፡10፤ዘሌዋውያን 1፡3-5፤4፡20-21፤16፡6-22)   
    ለ. በአዲስ ኪዳን፡- የብሉይ ኪዳን የስርየት መስዋዕት እሳቤ በዋናነት ድጋፍ አግኝቷል፡፡ ነገር ግን የሰው ዘር ሁሉ ቤዛነት ሊፈጸም የሚችለው የእግዚአብሄር ልጅ የሆነውን የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ በማቅረብ ብቻ ነው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሐጢያቶቻችን እንደሞተ ተናግሮዋል፡፡ (1ኛ ቆሮንቶስ 15፡3)  
    ስርየት የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው የአዳምን ሐጢያት ለማስተሰረይ የሆነውን የክርስቶስን ሞት ለማመላከት ብቻ ሳይሆን የሰዎችን ሐጢያቶች በሙሉ ለመውሰድም ነው፡፡ የዓለም ሐጢያቶች ወደ ኢየሱስ ከተላለፉበት ጥምቀት በኋላ (ማቴዎስ 3፡15) እርሱ በመስቀል ላይ ደሙን በማፍሰስ የሰውን ዘር ሁሉ አዳነ፡፡ (ዘሌዋውያን 1፡1-5፤ዮሐንስ 19፡30)   
    ሐዋርያው ጳውሎስ በ2ኛ ቆሮንቶስ 5፡14 ላይ ‹‹አንዱ ስለ ሁሉ እንደሞተ›› ያብራራና ከዚያም በቀጣዩ ቁጥር 21 ላይ ይህም ‹‹ስለ እኛ›› እንደነበር ያወሳል፡፡ በገላትያ 3፡13 ላይም እንደዚሁ ‹‹ስለ እኛ እርግማን ሆነ›› ይለናል፡፡ በአዲስ ኪዳን ውስጥ ኢየሱስን እንደ መስዋዕት የሚጠቁሙት ጥቂት ቁጥሮች ብቻ ናቸው፡፡ (ለምሳሌ፡- ኤፌሶን 5፡2) ዮሐንስ 1፡29,36 (‹በግ›-- አጥማቂው ዮሐንስ) እና 1ኛ ቆሮንቶስ 5፡7 (‹ፋሲካችን› --ሐዋርያው ጳውሎስ)፡፡    
    ነገር ግን ጳውሎስ ኢየሱስ በዮርዳኖስ የተቀበለው ጥምቀት ለዓለም ሁሉ ሐጢያቶች የሆነ ስርየት እንደነበር በግልጽ ያስቀምጣል፡፡ በሮሜ 6 ላይ የዓለም ሐጢያቶች በሙሉ በአጥማቂው ዮሐንስ በሆነው ጥምቀት አማካይነት ወደ ኢየሱስ እንደተላለፉ አብራርቷል፡፡ 
    እርሱ የኢየሱስ ስቅለት የሐጢያት ፍርድና ካሳ እንደነበር፤ የስርየት መስዋዕትም ለሰዎች ሁሉ ነፍስ እንደቀረበ ማብራራቱን ይቀጥላል፡፡ 
    የኢየሱስ ሞት በብሉይ ኪዳን የስርየት መስዋዕት የተመለከተው የእግዚአብሄር ዕቅድ መታወቂያ ነበር፡፡ በብሉይ ኪዳን የነበረው የእጆች መጫንና በአዲስ ኪዳን ያለው የኢየሱስ ጥምቀት በእግዚአብሄር ሕግ መሰረት የሆኑ ናቸው፡፤ (ኢሳይያስ 53፡10፤ ማቴዎስ 3፡13-17፤ዕብራውያን 7፡1-10,18፤ 1ኛ ጴጥሮስ 3፡21)     
    አዲስ ኪዳን በኢየሱስ ጥምቀትና ሞት አያበቃም፡፡ ነገር ግን የደህንነት ፍጻሜ አሮጌው ማንነታችን ከእርሱ ጋር ይሞት ዘንድ በሚያስችለን በክርስቶስ ውስጥ መጠመቅ እንደሆነ ይነግረናል፡፡ (ሮሜ 6፡3-7፤ገላትያ 2፡19-20) 
    አጥማቂው ዮሐንስ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ እንዲወስድ ኢየሱስ ክርስቶስን እንዳጠመቀውና ከዚህ የተነሳም እንደተሰቀለ ይነግረናል፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ በጥምቀቱና በደሙ አማካይነት የዓለምን ሐጢያቶች ከማንጻቱም በላይ በሰው ዘር ፋንታ ቅጣትን በመቀበልና ስቃይን በመታገስ ከሰይጣን ሐይል አድኖን ወደ እግዚአብሄር ሐይል መልሶናል፡፡ 
    ስለዚህ የኢየሱስ ቤዛነት ሰዎች ወደ እግዚአብሄር እንዳይቀርቡ ያግዳቸው የነበረውን የሐጢያት ችግር ፈቶዋል፡፡ ይህ ጠቃሚ ሁነት ደህንነትን፣ (ሮሜ 5፡11) ሕይወትን፣ (ሮሜ 5፡17-18) እና ቤዛነትን (ማቴዎስ 3፡15፤ዮሐንስ 1፡29፤ዕብራውያን 10፡1-20፤ ኤፌሶን 1፡7፤ ቆላስያስ 1፡14) በአንድ ጊዜ በማምጣት በሕዝቡና በእግዚአብሄር መካከል ሰላምንና ስምምነትን አመጣ፡፡     

  • 4. የስርየት ቀን 

    በዕብራይስጥ ይህ እሳቤ ‹የሽፋን› ወይም ‹የዕርቅ› ቀን ማለት ነው፡፡ ለአይሁዶች እጅግ አስፈላጊው ቀን በሰባተኛው ወር በአስረኛው ቀን የሚውለው የስርየት ቀን ነበር፡፡ (ዘሌዋውያን 23፡27፤25፡9) ሊቀ ካህኑም እንኳን በዚያ ቀን የሚደረጉትን ግልጽ የሆኑ ስርዓቶች ሳይፈጽም ወደ ቅድስተ ቅዱሳን መግባት እንደማይችል ከዘሌዋውያን 16 ማየት እንችላለን፡፡    
    ራሱ ቅድስተ ቅዱሳኑ እንደዚሁም የእስራኤል ሕዝብ ስርየት ያስፈልጋቸው ነበር፡፡ ስለዚህ ሊቀ ካህኑ እጆቹን በመስዋዕቱ ራስ ላይ በመጫን ሐጢያቶችን ለማስተላለፍ መስዋዕትን ማቅረብ ነበረበት፡፡ እስራኤሎች በስርየት ቀን ስለ እግዚአብሄር ቅድስናና ስለ ሐጢያቶቻቸው ያስቡ ነበር፡፡ 
    በዚያ ቀን 15 መስዋዕቶችን ያህል የበዙ፣ (የሚለቀቀውን ፍየል ጨምሮ) 12 የሚቃጠሉ መስዋዕቶችና 3 የስርየት መስዋዕቶች ለእግዚአብሄር ይሰዉ ነበር፡፡ (ዘሌዋውያን 16፡5-29፤ ዘሁልቁ 29፡7-11) በዙልቁ 28፡8 ላይ የተጠቀሰውን ‹ሌላውን ጠቦት› ከቆጠርን 13 የሚቃጠሉ መስዋዕቶችና 4 የስርየት መስዋዕቶች ይኖራሉ፡፡     
    እስራኤል የዓመቱን ሐጢያቶች ለማስተሰረይ የሚጠቀሙበት ቀን ሰባተኛው ወር አስረኛው ቀን ነበር፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታም ለዓለም ሁሉ የሚሆነው የስርየት ቀን ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ የተጠመቀበት ቀን ነበር፡፡ ይህ በእርግጥም ለሰው ዘር ሁሉ የስርየት ቀን ነው፡፡ ይህ ቀን እግዚአብሄር የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ያስወገደበት ቀን ነው፡፡ (ማቴዎስ 3፡13-17) እግዚአብሄር ‹‹እንዲህ…ጽድቅን ሁሉ የፈጸመበት›› የስርየት ቀን ነበር፡፡  

  • 5. የስርየት መስዋዕት 

    በብሉይ ኪዳን፡- ልክ እንደ ሌሎቹ መስዋዕቶች ሁሉ እስራኤሎችን ሁሉ የሚቀድሰው የቅድስና መስዋዕት በመገናኛው ድንኳን ውስጥ ይቀርብ ነበር፡፡ ሊቀ ካህኑ ራሱን አንጽቶ ስርዓቶችን ለማከናወን በሚለብሳቸው የተለመዱ መደበኛ ልብሶች ፋንታ ቅዱስ የሆኑትን የበፍታ መጎናጸፊያዎች ይለብሳል፡፡ ለእርሱና ለቤተሰቡም የሐጢያት ቁርባን ይሆን ዘንድ ወይፈን፣ የሚቃጠል መስዋዕት ይሆን ዘንድም አውራ በግ ይመርጣል፡፡ (ዘሌዋውያን 16፡3-4) ሊቀ ካህኑ የሕዝቡን ዓመታዊ ሐጢያቶች ለማስተላለፍ እጆቹን በመስዋዕቶቹ ራስ ላይ ይጭናል፡፡ 
    እጆችን መጫን የስርየት ቀን አስፈላጊው ክፍል ነበር፡፡ ይህ ባይከናወን ኖሮ መስዋዕቶችን ማቅረብ አይከናወንም ነበር፡፡ ምክንያቱም የሐጢያት ስርየት ያለ እጆች መጫን ሊፈጸም ስለማይችል የእስራኤሎችን ዓመታዊ ሐጢያቶች ወደ ሐጢያት መስዋዕቱ ማስተላለፍም አይከናወንም ነበር፡፡ 
    በዘሌዋውያን 16፡21 ላይ ‹‹አሮንም ሁለቱን እጆቹን በሕያው ፍየል ራስ ላይ ይጭናል፡፡ በላዩም የእስራኤልን ልጆች በደል፣ ሁሉ መተላለፋቸውንም ሁሉ፣ ሐጢአታቸውንም ሁሉ ይናዘዛል፡፡ በፍየሉም ራስ ላይ ያሸክመዋል፡፡ በተዘጋጀውም ሰው እጅ ወደ ምድረ በዳ ይሰድደዋል›› ይላል፡፡   
    እርሱ የሐጢያት መስዋዕቶች ይሆኑ ዘንድ ሁለት ፍየሎችን፣ የሚቃጠል መስዋዕት ይሆን ዘንድም አንድ አውራ በግ (ዘሌዋውያን 16፡5) ወሰደ፡፡ ከዚያም በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ላይ በጌታ ፊት ሁለት ፍየሎችን ያቀርብና አንዱን ‹ለእግዚአብሄር› ሌላውን ‹ለሚለቀቅ› አድርጎ ለመለየት ዕጣዎችን ይጥላል፡፡  
    ለጌታ የሆነው ፍየል የሐጢያት መስዋዕት ሆኖ ይቀርብ ነበር፡፡ የሚለቀቀው ፍየልም የእስራኤልን ሕዝብ ዓመታዊ ሐጢያቶች ለማስተሰረይ በጌታ ፊት ሕያው ሳለ ይቀርብና ከዚያም ወደ ምድረ በዳ ይሰደዳል፡፡ (ዘሌዋውያን 16፡7-10) 
    የእስራኤል ሐጢያቶች በሊቀ ካህኑ እጆች መጫን ወደሚለቀቀው ፍየል መተላለፍ ነበረባቸው፡፡ ከዚያም የእስራኤልን ሐጢያቶች በሙሉ በራሱ ላይ የወሰደው የሚለቀቀው ፍየል ሕዝቡና እግዚአብሄር ይታረቁ ዘንድ ወደ ምድረ በዳ ይሰደዳል፡፡ በዚህም የእስራኤል ዓመታዊ ሐጢያቶች ይሰረዩ ነበር፡፡ 
    በአዲስ ኪዳን፡- በተመሳሳይ መንገድ ኢየሱስ ክርስቶስ በአጥማቂው ዮሐንስ (በብሉይ ኪዳን እጆች መጫን) ተጠመቀ፡፡ የእግዚአብሄርን ማዳን የሚፈጽም የመስዋዕት በግ ሆኖ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ወሰደ፡፡ (ዘሌዋውያን 20፡22፤ ማቴዎስ 3፡15፤ ዮሐንስ 1፡29,36)  
    በብሉይ ኪዳን ዕጣዎቹ ከመጣላቸው በፊት አሮን ለራሱና ለቤተሰቡ ወይፈኑን ያርዳል፡፡ (ዘሌዋውያን 16፡11) ከዚያም በጌታ ፊት ካለው መሰውያ ላይ በተወሰደ የእሳት ፍም የተሞላ ጥና ወስዶ ከተወቀጠው ከጣፋጭ ዕጣን እጁን ሙሉ ይወስድና ከመጋረጃው በስቲያ ይዞት ይገባል፡፡ ከዚያም የዕጣኑ ጢስ በስርየት መክደኛው ላይ ይሰፍፍ ዘንድ በጌታ ፊት ዕጣኑን በእሳቱ ላይ ይጨምረዋል፡፡ ከወይፈኑም ደም የተወሰነውን ይወስድና በስርየት መክደኛው ላይ ሰባት ጊዜ በጣቱ ይረጨዋል፡፡ (ዘሌዋውያን 16፡12-19) 
    አሮን በስርየት ቀን በመስዋዕቶቹ ራስ ላይ የሚጭናቸው እጆቹ መቋረጥ የለባቸውም፡፡ አሮን እጆቹን በፍየሉ ራስ ላይ ጭኖ የእስራኤልን ሐጢያቶችና በደሎች ሁሉ በራሱ ላይ ያስተላልፋል፡፡ ከዚያም ፍየሉ በተመረጠው ሰው እጅ ወደ ምድረ በዳ ይወሰድና ይለቀቃል፡፡ የሚለቀቀው ፍየል የእስራኤልን ሐጢያቶች ይዞ በምድረ በዳ ይቅበዘበዝና በመጨረሻም ለእነርሱ ሲል ይሞታል፡፡ በብሉይ ኪዳን ዋናው የስርየት መስዋዕት ይህ ነበር፡፡ 
    ይህ በአዲስ ኪዳንም የሚለቀቀው ፍየል በጥምቀቱ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ በወሰደው፣ ስለ ሁላችንም በመስቀል ላይ ደሙን ባፈሰሰውና በሞተው በኢየሱስ ክርስቶስ ከመተካቱ በቀር ተመሳሳይ ነው፡፡   
    ስለዚህ አሁን ከሐጢያቶች ሁሉ መዳን ሰማያዊ ሊቀ ካህን ከሆነው ከኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀትና ስቅለት ውጭ ሊመጣ አይችልም፡፡ ከውሃና ከመንፈስ ዳግም የመወለድ ደህንነት ፍጻሜ ይህ ነው፡፡ 

  • 6. እጆችን መጫን፤ ሹመት 

    በብሉይ ኪዳን ሐጢያትን ለማስተላለፍ እግዚአብሄር የሰጠው ዘዴ ይህ ነበር፡፡ (ዘሌዋውያን 4፡29፤ 16፡21) በብሉይ ኪዳን ዘመን እግዚአብሄር ሰዎች በመገናኛው ድንኳን ውስጥ እጆቻቸውን በሐጢያት መስዋዕቶች ራሶች ላይ በመጫን ሐጢያቶቻቸውን እንዲያስተሰርዩ ፈቅዶላቸዋል፡፡ ይህም በአዲስ ኪዳን የሚመጣውን የኢየሱስን ጥምቀት ለመግለጥ ነበር፡፡   

  • 7. ጥምቀት 

    ጥምቀት ማለት ① መታጠብ ② መቀበር (መጥለም) በመንፈሳዊ ትርጉምም ③ በብሉይ ዘመን እንደተደረገው እጆችን በመጫን ሐጢያትን ማስተላለፍ ማለት ነው፡፡
    በአዲስ ኪዳን ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ የተጠመቀው የዓለምን ሐጢያት በሙሉ ለማንጻት ነበር፡፡ ‹የኢየሱስ ጥምቀት› የሰውን ዘር ሁሉ ሐጢያቶች የመውሰድና የዓለምን ሐጢያቶች የማንጻት ትርጉም አለው፡፡  
    ኢየሱስ የሰዎች ሁሉ ወኪልና ከአሮን የዘር ግንድ በሆነው ሊቀ ካህን በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ በራሱ ላይ ወስዶዋል፡፡ የእርሱ ጥምቀት አላማው ይህ ነበር፡፡  
    ‹ጥምቀት› የሚለው ቃል መንፈሳዊ ትርጉም ‹ማስተላለፍ፣ መቀበር› ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ‹‹የኢየሱስ ጥምቀት›› ማለት የዓለም ሐጢያቶች በሙሉ ወደ ኢየሱስ ተላልፈዋል፤ እርሱም በእኛ ፋንታ ተኮንኖዋል ማለት ነው፡፡ ኢየሱስ የሰውን ዘር ለማዳን ሲል በጥምቀቱ ሐጢያቶቻችንን መውሰድና ለእነርሱም መሞት ነበረበት፡፡ 
    ስለዚህ የእርሱ ሞትም እንደዚሁ የእናንተና የእኔ የዓለም ሐጢያተኞችም ሁሉ ሞት ነው፡፡ የእርሱ ትንሳኤም የሰዎች ሁሉ ትንሳኤ ነው፡፡ የእርሱ መስዋዕትነት የሐጢያተኞች ደህንነት ነው፡፡ የእርሱ ጥምቀት የሰው ዘር ሐጢያቶች በሙሉ ለመወገዳቸው ዋና ምስክር ነው፡፡  
    መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹ጥምቀት ምሳሌው ሆኖ አሁን ያድነናል›› (1ኛ ጴጥሮስ 3፡21) ይላል፡፡ የኢየሱስ ጥምቀት ሐጢያቶቻችንን በማስወገድ ሰዎችን ሁሉ የማዳኛው የጽድቅ መንገድ፡፡ 
     ኢየሱስ የሰዎች ሁሉ ወኪልና ከአሮን የዘር ግንድ በሆነው ሊቀ ካህን በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ በራሱ ላይ ወስዶዋል፡፡ የእርሱ ጥምቀት አላማው ይህ ነበር፡፡

  • 8. ሐጢአት 

    እግዚአብሄርን የሚቃወም ነገር ሁሉ ሐጢያት ነው፡፡ ይህ የአዳምን ሐጢያትና እኛ በሕይወት ዘመናችን ሁሉ የምንሰራቸውን መተላለፎች ጨምሮ ሐጢያቶችን ሁሉ ይመለከታል፡፡  
    ሐጢያት በግሪክ ‹ሐማርትያ› ነው፡፡ ግሳዊ መልኩም ‹ሐማርታኖ› ሲሆን ትርጓሜውም ‹ኢላማን መሳት› ነው፡፡ ስለዚህ እጅግ አስከፊ ከሆኑት ሐጢያቶች አንዱ በተሳሳተ መንገድ በኢየሱስ ማመንና የመዳን አቅም ማጣት ነው፡፡ እውነትን አለማወቅም ሆነ አለማመን የአለመታዘዝን ሐጢያት መስራትና እግዚአብሄርን መሳደብ ነው፡፡  
    በእግዚአብሄር ፊት በእውነት እንዲህ ያለ ሐጢያት መስራት የማንፈልግ ከሆነ የእርሱን ቃሎች በትክክል መረዳትና ኢየሱስ አዳኛችን የመሆኑን እውነት መገንዘብ ይኖርብናል፡፡ 
    በእግዚአብሄር ቃሎች አማካይነት የኢየሱስን ጥምቀትና መስቀሉን ማመን ይገባናል፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል አለመቀበል፣ ከእውነት ማፈንገጥና የሐሰት ጽንሰ አሳቦችን ማመን ሐጢያት ነው፡፡ 
    መጽሐፍ ቅዱስ ‹ወደ ሞት የሚመራው ሐጢያት› (1ኛ ዮሐንስ 5፡16) ማለትም እጅግ አደገኛው ሐጢያት እግዚአብሄር የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ እንዳስወገደ አለማመን እንደሆነ ይነግረናል፡፡ በኢየሱስ ውልደት፣ በጥምቀቱ አማካይነት ሐጢያትን ማስወገዱንና ደሙን በመስቀል ላይ በማፍሰስም ሕይወቱን ለእኛ መስጠቱን ማመን ይኖርብናል፡፡ አንድ ሰው ኢየሱስ እኛን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ለማላቀቅ እንደተጠመቀ፣ በመስቀል ላይ እንደሞተና እንደተነሳ በሚናገሩት የተጻፉ ቃሎች የማያምን ከሆነ ሐጢያት ነው፡፡  

  • 9. ንስሐ 

    ከእግዚአብሄር የራቀ ሰው ሐጢያቶቹን ተገንዝቦ ኢየሱስ እንዳስወገዳቸው እርሱን በማመስገን ወደ እግዚአብሄር ሲመለስ ይህ ንስሐ ተብሎ ይጠራል፡፡
    ሁላችንም የሐጢያት ክምሮች ነን፡፡ እውነተኛ ንስሐ ቀጣዩን እውነት መቀበል ነው፡፡ እኛ በእግዚአብሄር ፊት ሐጢያተኞች እንደሆንን፣ በሕይወት ዘመናችን ሁሉ ሐጢያት እንደምንሰራና ስንሞት ሲዖል እንደምንወርድ፣ ኢየሱስ እንደ እኛ አይነት ሐጢያተኞችን ለማዳን ወደዚህ ዓለም እንደመጣ በማመን እርሱን አዳኛችን አድርገን መቀበል እንደሚኖርብን፣ እኛን ለማዳንም ሐጢያቶችን ሁሉ (በጥምቀቱ አማካይነት) እንደወሰደ፣ እንደሞተና እንደተነሳ ማመን አለብን፡፡ እውነተኛ ንስሐ የራሳችንን አስተሳሰቦች መተውና ወደ እግዚአብሄር መመለስ ነው፡፡ (የሐዋርያት ሥራ 2፡38)     
    ንስሐ ሐጢያቶቻችንን ማመንና ከሙሉ ልባችንም የውሃውንና የደሙን ደህንነት ለመቀበል ወደ እግዚአብሄር ቃል መመለስ ነው፡፡ (1ኛ ዮሐንስ 5፡6) 
    እውነተኛ ንስሐ እኛ ፈጽመን ሐጢያተኞች መሆናችንን መቀበልና የእግዚአብሄርን ልጅ ኢየሱስን አዳኛችን አድርገን ማመን ነው፡፡ ለመዳንና ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ለመንጻት በራሳችን ሥራዎች አማካይነት መቀደስ መሞከርን ማቆምና እኛ በእግዚአብሄርና በሕጎቹ ፊት ፈጽመን ሐጢያተኞች መሆናችንን ማመን አለብን፡፡ ከዚያም ኢየሱስ በጥምቀቱና በደሙ የሰጠንን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ማለትም የደህንነቱን እውነት መቀበል ይኖርብናል፡፡   
    አንድ ሐጢያተኛ የራሱን አስተሳሰቦች ሁሉ መተውና ፈጽሞ ወደ ኢየሱስ መመለስ አለበት፡፡ የኢየሱስ ጥምቀት ሐጢያቶቻችንን በሙሉ በራሱ ላይ የወሰደበት እንደሆነ ወደ ማመን ስንመጣ እንድናለን፡፡ 
    በሌላ አነጋገር የኢየሱስ ጥምቀት፣ ስቅለቱና ትንሳኤው ለሐጢያተኞች ሁሉ ደህንነት የእግዚአብሄርን ጽድቅ ፈጽመዋል፡፡ ኢየሱስ በሥጋ መጣ፡፡ ሐጢያቶቻችንን ሁሉ ለማስወገድም ተጠመቀ፤ ተሰቀለ፡፡ እውነተኛ ንስሐና ትክክለኛ እምነት በእነዚህ ሁሉ ላይ ሙሉ እምነት መያዝና ኢየሱስ በእርሱ ለሚያምኑ ሁሉ አዳኝ ለመሆን እንደተነሳ ማመን ነው፡፡  

  • 10. ደህንነት

    በክርስትና ውስጥ ደህንነት ማለት ‹ከሐጢያት ሐይል ወይም ቅጣት መዳን› ማለት ነው፡፡ ለሐጢያቶቻችን ሲዖል እንደምንወርድ ስንቀበልና ኢየሱስ በውልደቱ፣ በጥምቀቱና በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደሙ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ እንዳዳነን ስናምን ደህንነትን እንቀበላለን፡፡   
    በኢየሱስ ደህንነት፣ በኢየሱስ ጥምቀትና ደም በማመን ሐጢያት አልባ የሆኑ ሰዎች ‹የዳኑ፣ ዳግም የተወለዱና ጻድቃን› ተብለው ይጠራሉ፡፡ 
    ‹ደህንነት› የሚለውን ቃል በኢየሱስ በማመን የአዳምን ሐጢያትና በየቀኑ የሚሰሩዋቸውን ሐጢያቶች ጨምሮ ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ ለዳኑ ሰዎች ልናውለው እንችላለን፡፡ እየሰመጠ ያለው ሰው እንደሚድን ሁሉ በዓለም ሐጢያት ውስጥ እየሰጠመ ያለ ሰውም ኢየሱስን አዳኙ አድርጎ በማመን የመንፈሳዊ እውነት ቃሎች በሆነው የእርሱ ጥምቀትና ደም በማመን መዳን ይችላል፡፡  

  • 11. ዳግም መወለድ 

    ይህ ማለት ‹ለሁለተኛ ጊዜ መወለድ› ማለት ነው፡፡ አንድ ሐጢያተኛ ዳግም የሚወለደውና ጻድቅ የሚሆነው በኢየሱስ ጥምቀትና በመስቀሉ በማመን በመንፈሳዊ መልኩ ሲድን ነው፡፡  
    በኢየሱስ ጥምቀትና ደም በማመን በመንፈሳዊ መልኩ ዳግም መወለድ እንችላለን፡፡ ዳግም የተወለዱ ሰዎች ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ የነጹና ‹‹ያድናቸው ዘንድ ሁለተኛ ጊዜ ያለ ሐጢአት ይታይላቸው ዘንድ እርሱን የሚጠባበቁት›› ናቸው፡፡ (ዕብራውያን 9፡28) 

  • 12. የሐጢያቶች ስርየት 

    ይህ ጠቃሚ እሳቤም እንደዚሁ የሐጢያቶች ይቅርታ ተብሎ ይታወቃል፡፡ እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት ለአንዴና ለመጨረሻ ከሐጢያቶች ሁሉ ስንነጻ ሐጢያቶች ይቅር ይባላሉ፡፡ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እምነት ቅጥልጣል በሆኑ እውነቶች ማመን ነው፡፡ እነዚህም የኢየሱስ ክርስቶስ መለኮታዊነት፣ የእግዚአብሄር ልጅ ሥጋ መልበስ፣ ለሁላችንም ደህንነት የሆኑት የእርሱ ጥምቀት፣ ስቅለትና ትንሳኤ ናቸው፡፡  
    ኢየሱስ የሰጠን ቤዛነት በእርሱ ጥምቀትና ደም በማመን የእኛ ሊሆን ይችላል፡፡ በብሉይ ኪዳን ውስጥ እንደተተነበየው ኢየሱስ ራሱ ሰዎችን ሁሉ ከሐጢያት አድኖዋቸዋል፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያለው ቤዛነት በኢየሱስ ጥምቀትና ደም ላይ ባለው እምነት አማካይነት የሆነውን የሐጢያቶች መንጻት ይጠቁማል፡፡ ሐጢያቶች በሙሉ ወደ ኢየሱስ ተላልፈዋል፡፡ ስለዚህ ከእንግዲህ ወዲህ በሰው ዘር ልብ ውስጥ ሐጢያት የለም፡፡    
    ራሳችንን የዳንንና ጻድቃን ብለን መጥራት የምንችለው በእርሱ ጥምቀት ላይ ባለን እምነት አማካይነት ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ወደ ኢየሱስ ስናስተላልፍ ብቻ ነው፡፡ 

  • 13. ኢየሱስ ክርስቶስ

    ኢየሱስ፡- ‹ሰዎችን ሁሉ ከሐጢያቶቻቸውና ከእነዚያም ሐጢያቶች ቅጣት ያዳነ አዳኝ፡፡› ኢየሱስ የሚያመላክተው ሰዎችን ሁሉ ከሐጢያቶቻቸው ያዳነውን አዳኝ ነው፡፡
    ክርስቶስ፡- ‹የተቀባ፡፡› በእግዚአብሄር ፊት በሥራ ማዕረጎች ላይ መቀባት የነበራቸው ሦስት አይነት ሰዎች ነበሩ፡፡   ① ነገሥታት   ② ነቢያት እና ③ ካህናት፡፡ ኢየሱስ ሁሉንም ፈጽሞዋል፡፡  
    ኢየሱስ ክርስቶስ እነዚህን ሁሉ ነበር፡፡ የእነዚህን ሥራ ሁሉ ሰርቷል፡፡ ኢየሱስ ቤዛነትንና ደህንነትን ያመጣልን ንጉሥ፣ ነቢይና ካህን እንደሆነ ማመን አለብን፡፡ ስለዚህ ‹ኢየሱስ ክርስቶስ› ብለን እንጠራዋለን፡፡ እርሱ በጥምቀቱና በደሙ ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ ያዳነን ሰማያዊ ሊቀ ካህን ነበር፡፡    
    ስለዚህ እርሱ በእርሱ ለሚያምኑ ሁሉ ንጉሥ ነው፡፡ በፊቱ ስንቀርብ ሐጢያቶቻችንን እንድንገነዘብ ያደርገናል፡፡ ከቅድመ አያቶቻችን ጀምሮ ሐጢያተኞች እንደሆንን የሐጢያተኞች ዘሮች በመሆናችንም ሐጢያተኞች ሆነን እንደተወለድንና ከዚህ የተነሳም ከእግዚአብሄር ፍርድ በታች እንደሆንን አስተምሮናል፡፡  
    በእርሱ ጥምቀትና ደም አማካይነትም ከሐጢያቶቻችን እንደነጻንም አስተምሮናል፡፡ እነዚህን ሥራዎች ሁሉ የሰራው ለእኛ ለሐጢያተኞች ነው፡፡ 

  • 14. የእግዚአብሄር ሕግ፡ አስርቱ ትዕዛዛት 

    በእግዚአብሄር ሕግ ውስጥ የቀን ተቀን ሕይወትን የሚመለከቱ 613 የሕግ አንቀፆች አሉ፡፡ ነገር ግን የእነዚህ መሰረት በእግዚአብሄር ፊት ልንጠብቃቸው ያሉት አስርቱ ትዕዛዛት ናቸው፡፡ ‹‹ይህንን አድርግ›› ‹‹ያንን አታድርግ›› የሚሉ ትዕዛዞችና ክልከላዎች አሉ፡፡ እነዚህ የኑሮ መመሪያዎች ናቸው፡፡ የእግዚአብሄር ትዕዛዛት የተሰጡን ሐጢያቶቻችንን እንድናውቅ ነው፡፡ በተጻፉት የእግዚአብሄር ትዕዛዛቶች አማካይነት ምን ያህል እርሱን እንደማንታዘዘው መገንዘብ እንችላለን፡፡ (ሮሜ 3፡19-20)   
    እግዚአብሄር ትዕዛዛቱን የሰጠበት ምክንያት ሐጢያቶቻችንን እንድንገነዘብ ነው፡፡ የእርሱን ትዕዛዛቶች በሙሉ በፍጹም መጠበቅ አንችልም፡፡ ስለዚህ በኢየሱስ ከማመናችን በፊት ሐጢያተኞች የመሆናችንን እውነት በትህትና መቀበል አለብን፡፡ እኛ ሁላችን ሐጢያተኞች ነን፡፡ እግዚአብሄርም በእርሱ ሕግ መሰረት ፈጽሞ መኖር እንደማንችል ያውቃል፡፡ ስለዚህ ሰው ሆኖ ወደዚህ ዓለም መጣ፤ ተጠመቀ፤ በመስቀል ላይም ተኮነነ፡፡ በእርሱ ትዕዛዛቶች ለመኖር መሞከር የዕብሪት ሐጢያት ነው፡፡ ያንን ማድረግ አይገባንም፡፡   
    ሕጉ እግዚአብሄር ምን ያህል ፍጹምና ቅዱስ እንደሆነና ሰዎችም በእርግጥ ምን ያህል ደካሞች እንደሆኑ ያሳየናል፡፡ በሌላ አነጋገር የእግዚአብሄር ቅድስናና ፍጽምና በእግዚአብሄር ሕግ ውስጥ ተገልጦዋል፡፡ 

  • 15. ኢየሱስ የተጠመቀበት የዮርዳኖስ ወንዝ 

    የዮርዳኖስ ወንዝ በፍጥነት ወደ ሙት ባህር ይፈስሳል፡፡ የሙት ባህር ወለል ከባህር ጠለል በ400 ሜትር ዝቅ ያለ ነው፡፡ ስለዚህ የሙት ባህር ውሃ ወደ የትም ስፍራ መፍሰስ አይችልም፡፡ በሙት ባህር ውስጥ የተቆለፈ ነው፡፡  
    የሙት ባህር ጨዋማና ሌሎች ተራ ባህሮች ካላቸው የጨውነት ባህርይ 10 ጊዜ ያህል ከፍተኛ ነው፡፡ በዚያ ውስጥ ምንም አይነት ፍጥረት አይኖርም፡፡ ስለዚህ የሙት ባህር ተብሎ ተጠራ፡፡ ኢየሱስ በሞት ባህር (በዮርዳኖስ ወንዝ) ውስጥ በአጥማቂው ዮሐንስ ተጠመቀ፡፡ ይህም በልባቸው ውስጥ ሐጢያት ከሌለባቸው ሰዎች ውጭ ያሉ ሰዎች በመጨረሻ ለሐጢያቶቻቸው የዘላለም ኩነኔን እንደሚቀበሉ ያመላክታል፡፡    
    ስለዚህ የዮርዳኖስ ወንዝ ሐጢያቶች የሚነጹበት፤ ሐጢያተኞችም የሚሞቱበት ወንዝ ነው፡፡ በአጭሩ የዓለም ሐጢያቶች በሙሉ ወደ ኢየሱስ በተላለፉበት የእርሱ ጥምቀት አማካይነት የተላለፉበት የቤዛነት ወንዝ ነው፡፡
    ኢየሱስ በሞት ባህር (በዮርዳኖስ ወንዝ) ውስጥ በአጥማቂው ዮሐንስ ተጠመቀ፡፡