Search

መልዕክቶች ከአጋር ሠራተኞች፤

አጋር ሠራተኛ ከሆንክና "መልዕክቶች ከአጋር ሠራተኞች" በሚለው ላይ መልዕክትና ፎቶዎችን መለጠፍ የምትወድ ከሆነ "መልዕክት ለጥፍ" የሚለውን ቁልፍ ጠቅ አድርግና ግባ፡፡ ልጥፍህ የሚታየው የእኛን ይሁንታ ሲያገኝ ብቻ ይሆናል፡፡

መልዕክት ለጥፍ
ጠቅላላ፤ 12
  • ቁ.7

    ወደ ውሃውና መንፈሱ ወንጌል ተመለሱ

    ወደ እግዚአብሔር መንግስት የምንገባበት አንድ ብቸኛ መንገድ አለ! እንዲሁም እውነተኛ ያልሆኑ ግን እውነትኛ የሚመስሉ የሀሰት መንገዶችም አሉ! ታዲያ የሰው ልጅ ሁሉ ወደ እግዚአብሔር መንግስት የሚወስደውን እውነተኛውን መንገድ በእግዚአብሔር ቃል መሰረት ማግኘትና በዛም ማመን አለበት! መጽሀፍ ቅዱስ በዩሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 3፥5 ላይ ሰው ከውሃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግስት እንደማይገባ ተጽፏል! ስለዚህ በእግዚአብሔር ቃል መሰረት ማንም ሰው ወደ እግዚአብሔር መንግስት ለመግባት ከውሃና ከመንፈስ መወለድ አለበት! ይህ መጽሀፍ ስለውሃና መንፈስ ወንጌል መንፈሳዊ ትርጉም እንዲሁም የዘመኑን የሀሰት ወንጌልና እውነተኛውን ወንጌል  በእግዚአብሔር ቃል መሰረት በግልጽ የሚዳስስ የቄስ ፓውል ሲ ጆንግ ሁለተኛ እትም መጽሀፍ ነው!መጽሀፉ ስምንት ስብከቶች ያሉት ሲሆን በመጀመሪያው ስብከት  በዩሐንስ 3፥1-6 መሰረት እውነተኛ ዳግም የመወለድ ወንጌል ትርጉምን ያስረዳል!  ዳግመኛ ስለመወለድ መንፈሳዊ ሚስጢር ስንገነዘብ የሰው ልጅ ሁሉ ከእድሜ ልክ ኅጢአቱ የሚነጻበትን እውነታ እናገኛለን፡ ያም እውነት ከውሃና ከመንፈስ ዳግም መወለድ ማለት ነው፡፡ በሌላ አገላለጽ እውነተኛ የእግዚአብሔር ልጅ መሆን ማለት ነው። ውሃ ማለት የኢየሱስ ጥምቀት ሲሆን መንፈስ ማለት የእርሱ አምላክነት ማለት ነው። ስለዚህ ከውሃና ከመንፈስ ዳግም ለመወለድ ማናችንም ኢየሱስ ክርስቶስ በጥምቀቱ የዓለምን ኅጢአት ሁሉ መሸከሙን ስለዛም ኅጢአት ዋጋን ሁሉ እስከሞት ድረስ መክፈሉን ከሞትም መነሳቱን እንዲሁም ይህን ታላቅ ስራ ለሰው ልጅ ሁሉ በእኩል ያደረገው ኢየሱስ አምላክ መሆኑን ማመን አለብን!በሁለተኛው ስብከት በኢሳያስ 28፥13-14 መሰረት በክርስትና ውስጥ ስላሉ አስመሳይ ክርስቲያኖችና መናፍቃን በስፋት ተብራርቷል! ከውሃና ከመንፈስ ዳግም ያልተወለደ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት መናፍቅ ነው! በሌላ አነጋገር በክርስቶስ አምናለው እያለ በልቡ ኅጢአት ያለበት ሰው ሁሉ እርሱ መናፍቅና አስመሳይ ክርስቲያን ነው! እነዚህ አስመሳይ ክርስቲያኖች ለሰዎች በትክክል ዳግም የሚወለዱበትን ወንጌል ሊሰብኩ አይችሉም! ስብከታቸው ሁሌም ስለቁሳዊ ነገሮችና ስለሰው ልጅ አስተሳሰብ ብቻ ነው! እነዚህ መናፍቃን በእርግጥም የእግዚአብሔር ፍርድ ይጠብቃቸዋል! እውነተኛ ክርስቲያኖች የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል አማኞች ብቻ ናቸው! እነርሱም ስለኢየሱስ አምላክነት፡ ጥምቀት፡ ሞትና ትንሳኤ በግልጽ የሚሰብኩ ሁሉም ሰው ከሀሰተኛ ነብያቶች ራሳቸውን እንዲጠብቁ የሚያስተምሩ ድንቅ የክርስቶስ አገልጋዮች ናቸው!በሶስተኛው ስብከት በዘጸአት 12፥43-49 መሰረት ስለእውነተኛው መንፈሳዊ ግርዘት በስፋት ተብራርቷል! በብሉይ ኪዳን ፋሲካን ማክበር የሚፈልግ ማንኛውም ሰው መገረዝ አለበት! ፋሲካ ማለት እስራኤለውያን ከግብጽ የባርነት ህይወት ነጻ የወጡበትን ጊዜ የሚያስታውሱበት እና እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑበት በዓል ሲሆን በዓሉንም ለማክበር የመገረዝ ግዴታ ነበረባቸው! በአዲስ ኪዳን ስንመጣ ማንም በክርስቶስ ማመንና የእርሱ ልጅ መሆን የሚችለው በልቡ ሲገረዝ ነው፡፡ መጽሀፍ ቅዱስ በሮሜ 2፥29 ላይ መገረዝ የልብ እንደሆነ ይናገራል፡፡ ያም ማለት እስራኤልቅውያን ሸለፈታቸውን ቆርጠው በመጣል የእግዚአብሔር ህዝብ እንደሚሆኑት ሁሉ እኛም በክርስቶስ ጥምቀት ስናምን ወይም ኅጢአቶቻችንን ሁሉ በእምነት ወደ ኢየሱስ ስናሻግር የእርሱ እውነተኛ ልጆች እንሆናለን ማለት ነው!አራተኛው ስብከት በ1ኛ ዩሐንስ 1፥9 በኩል እውነተኛውና ትክክለኛው ኑዛዜ እንዴት እንደሚደረግ ይነግረናል! ይህን ክፍል ዳግም ያልተወለዱ ሰዎች በተሳሳተ መንገድ ይረዱትና በንስሀ ጸሎቶቻቸው ከኅጢአቶቻቸው ለመንጻት ይሞክራሉ! እውነታው ግን ማንም ሰው በንስሀ ጸሎት ኅጢአትን የማስወገድ ስልጣን የለውም የሚል ነው፡፡ ምክንያቱም ኅጢአትን የማስውውገድ ስልጣን ያለው ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው፡፡ በልባችሁ ኅጢአት ያለባችሁ ማናችሁም ለመዳን ብትወዱ የሚከተልውን ኑዛዜ ማድረግ ይኖርባችኋል! ጌታ ሆይ እኔ ኅጢአቶቼ በዝተዋል ሞትም ይገባኛል፡፡ አንተ ካላዳንከኝ በእርግም እሞታለው! ዘወትር ይቅር በለኝ በማለት እጸልያለው ነገር ግን ከኅጢአቶቼ ሁሉ መንጻት አልቻልኩም እባክህ አባት ሆይ አድነኝ እራራልኝም! በንጹህ ልብ ይህን ካደረጋችሁ እግዚአብሔር በአግልጋዮቹ አማካኝነት የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ይገልጥላችኋል! የክርስቶስ ልጅ ከሆንን በኋላ እንደሚከተለው እንናዘዛለን ጌታሆይ ስጋዬን የመከተል ኅጢአት ሰርቻለው፡፡ አንተ በአጥማቂው ዩሐንስ ስትጠመቅ ያለፈውን አሁን የፈጸምኩትን እና የወደፊቱንም ኅጢአቴን ሁሉ እንዳስወገድክልኝ አምናለው! ያ ባይሆን እሞት ነበር! በጥምቀትህ በሞትህና በትንሳኤክ ስላዳንከኝ አመሰግናለው! ዘወትር እንዲህ በመናዘዝ ጻድቃን ህይወታቸውን ይቀጥላሉ! የጻድቃን እና የኅጢአተኞች ኑዛዜ ይለያያል፡፡አምስተኛው ስብከት በሮሜ 8፥28-30 መሰረት አስከድሞ በመወሰንና በመልኮት ምርጫ ጽንስ ሀሳብ ውስጥ ስላለው ስዕተት ያብራራል! በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ላይ ትክክለኛ መረዳት ከሌለን በክርስቶስ ለማመን እንቸገራለን እንዲሁም ተመርጬ ይሁን ወይስ አይሁን በማለት ግራ መጋባት ውስጥ እንወድቃለን! እግዚአብሔር አስቀድሞ ከአዳም ጀምሮ የሰው ልጅ ሁሉ በኅጢአት እንደሚወድቅና ለዛም ቅጣት ፍርዱ ሞት ስለሆነ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ሊያድነን ወደደ ሁላችንም ማወቅ ያለብን እውነት እግዚአብሔር ያለምንም አድሎ ሁላችንንም በእኩል እንደወደደን መገንዘብ አለብን! ስለዚህ ሁላችንም ያለምንም አድሎ የወደደንን ጌታ በንጹህ ልባችን ማመን አለብን! ይህን በማድረግ ሃሰተኛ ሰባኪዎች በሚያስፋፉት የአስቅድሞ መወሰንና የመለኮት ምርጫ የተሳሳቱ አስተምህሮቶች ላይ እንዳንወድቅ መጠንቀቅ ይኖርብናል!ስድስተኛ ሰብከት በዕብራውያን 7፥1-28 መሰረት ስለተለወጠው ክዕነት ያስረዳል! የተለወጠውን ክዕነት በአግባቡ ለይተን ካላወቅን እምነታችን ሙሉ አይሆንም! ብዙዎች ይህን ባለማወቅ በብዙ ውንዥንብር ውስጥ ወድቀዋል! የተለወጠው ክዕነት ማለት በአጭሩ ሲገልጽ በብሉይ ኪዳን የነበረውን የስርየት ስርዓትን በመሻር በአዲስ ኪዳን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጅ ሁሉ በእኩል የሰራው ጽድቅ ማለት ነው! በብሉይ ኪዳን ለስርየት የሚቀርበው መስዋዕት እለት እለት ወይም በቀጣይነት በአመት አንድ ጊዜ  የእስራኤለውያንን ኅጢአት በእጆች መጫን ስርዓት ይቀበላል ስለዛም ኅጢአት መስዋዕቱ ይሞታል! ነገር ግን ያ የስርየት የስርዓት ስርዓት ከእድሜ ልክ ኅጢአቶቻቸው አያነጻቸውም ነበር! የብሉይ ኪዳኑ መስዋዕት በአዲስ ኪዳን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የሚያመለክት ሲሆን ኢየሱስ ያለነውርና እንከን ወደ ምድር በመምጣት በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ በእጆች መጫን ስርዓት አማካኝነት የዓለምን ኅጢአት ሁሉ ተሸከመ ሰለዛም ኅጢአት በመስቀል ላይ ዋጋን ከፈለ! ሞተም በሶስተኛውም ቀን ከሞት ተነሳም! ሀሌሉያ!!!ሰባተኛው ስብከት ማቲዮስ 3፥13-17ን በመዳሰስ የኢየሱስ ጥምቀት ለቤዛነት አስፈላጊ የመሆኑን ሂደት ያብራራል! ማናችንም ከዕድሜ ልክ ኅጢአቶቻችን በመንጻት ከዘላለም ሞት መንዳን ብንወድ የግዴት በክርስቶስ ጥምቀት በኩል ማመን አለበን!!! (በዩሐንስ 1፡29) የዓለምን ኅጢአት የሚያስውግድ የእግዚአብሔር በግ የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእጆች መጫን ስርዓት በጥምቀቱ የእድሜ ልክ ኅጢአቶቻችንን ሁሉ በስጋው ተሸከመ! ስለበደላችንም በመስቀል ላይ ሞተ በሶስተኛውም ቀን ከሞት ተነሳ ሃሌሉያ! ለቤዛነታችን ከዚህ ውጭ ወንጌል የለም!!!በመጨረሻው ስብከት ማቲዮስ 7፡21-23ን እናገኛለን በዚህም ስብከት የአብን ፈቃድ በእምነት ስለመፈጸም እንማራለን! ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚል ሁሉ መአንግስተ ሰማያት የሚገቡ አይደሉም፡፡ ክፍሉ የእግዚአብሔርን ፍቃድ የሚያደርጉ ብቻ ወደ እግዚአብሔር መንግስት እንደሚገቡ ይናገራል! ስልዚህ የእግዚአብሔር ፍቃድ ምን እንደሆነ ሁሉም ሰው ማወቅ እና ማመን አለበት! ያም ፈቃድ ማለት እግዚአብሔር እኛን የሰው ልጆችን በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ከኅጢአቶቻችን ሁሉ በማንጻት የራሱ ልጆች ማድረጉ ነው! እግዚአብሔር ይመስገን ከውሃውና ከምንፈስ ዳግም በመወለዴ የክርስቶስ ልጅ ሆኛለው! ይህን ወንጌል በመስበክ የእግዚአብሔርን ፈቃድ በእምነት እየፈጸምኩ ነው!ማናችሁም በዚህ መጽሀፍ ውስጥ ያሉትን መልዕክቶች በልባችሁ ብትቀበሏቸው ከሀሰተኛ ንብያት በመጠንቀቅ እውነተኛውን የወንጌል በር ታገኛላችሁ የክርስቶስ ደቀመዝሙርም ትሆናላችሁ!Teferi Oshine, Ethiopia

    • Teferi Oshine
    • Ethiopia
    • 08/04/202249
  • ቁ.6

    ወንጌልን ስንሰብክ በጥበብ ይሁን!

    ወንጌልን ስንሰብክ በጥበብ መስበክ እንዳለብን የእምነት አባቶቻችን ይመክሩናል! ያ እጅግ በጣም ድንቅ ምክር ነው! ወንጌልን በጥበብ መስበክ ማለት ከዕለት ዕለት ህይወትችን ስንነሳ ዳግም ካልተወለዱ ሰዎች ጋር በሚኖሩን የተለያዩ ግንኙነቶቻችን መልካም ግንኙነቶችን ማድረግ ይኖርብናል! ያም ወንጌልን በምንሰብካቸው ሰዓት ምቹ ሁኔታን ይፈጥርልናል! ሌላው ለዓለም ህጎችም መገዛት ይኖርብናል ምክንያቱም የዓለም ህጎችን ተላልፈን ወንጌልን መስበክ አይቻልምና! የዓለም ህጎችን መታዘዝ ስንል ግን ሁሉንም ህጎች መቀበል ማለት አይደለም! መታዘዝ ያለብን እምነታችንን የማይነኩ ሲሆኑ ብቻና ብቻ መሆን አለበት! የእምነት አባቶቻችን እምነታቸውን የሚነኩ የዓለም ህጎችን አንቀበልም በማለት ሰማዕት ሆነዋል! እኛም የዛሬዎቹ ጻድቃን በእምነታችን የሚመጣብንን ማንኛውንም ነገር መታዘዝም ሆነ መቀበል የለብንም! በሌላ በኩል ወንጌልን በጥበብ መስበክ ማለት ባገኘናቸው የወንጌል በሮች ሁሉ በመጠቀም ወንጌልን መስበክ አለብን ማለት ነው! በሌላ አነጋገር አቅማችን በፈቀደው ሁሉ ወንጌልን መስበክ አለብን ማለትም ነው! ሁላችንም እዚጋ አንድ ማስታዋል ያለብን ነገር ወንጌልን በየትኛው ዘርፍ መስበክ እንዳለብን ማወቅ አለብን ያም ማለት የትኛው ዘርፍ ወንጌልን ለመስበክ እንደሚቀርበን መገንዘብ ማለት ነው! በቸርች ውስጥ ወንጌልን በማሰራጨት ሂደት ላይ ከትናንሽ ሀላፊነቶች ጀምሮ እስከ ትላልቅ ሀላፊነቶች አሉ! ለምሳሌ ቤ/ክንን ማጽዳት, ለወንጌል ስርጭት መውጣት, የተለያዩ የጉልበት ስራዎችን መስራት, ለቅዱሳን ምግብ ማብሰል, ስብከቶችን መስበክ, ዝማሬዎችን ማዘጋጀት ሌሎችም የመሳሰሉ ስራዎች ይኖራሉ! አንድ ጻድቅ ሁሉንም ሀላፊነቶች ብቻውን መወጣት በፍጽም አይችልም ሁላችንም ግን የየራሳችንን ሀላፊነቶች ስናውቅ ሀላፊነቶቻችንን በአግባቡ መወጣት እንችላለን እዚጋ ዋናው መልዕክት አንዳችን ያለአንዳችን በጋራ ካልሆነ በቀር በግላችን በፍጥነት መራመድ አለመቻላችን ነው! እኛ ቅዱሳን ባለንበት ውስብስብ ዓለም ውስጥ የውሀውንና የመንፈሱን ወንጌልን በአራቱም ማዕዘናት የማሰራጨት ሃላፊነት አለብን ይሄን ስል የእኔ ሃላፊነት ምንድነው በየትኛውስ ዘርፍ ነው ማገልገል ምችለው? ጥያቄውን ለራሳችን እየመልስን በምንችለው ሁሉ ወንጌልን መስበክ ይኖርብናል! ሁላችንም ባለን አቅም በትጋት ወንጌልን የምንሰብክ ከሆነ በዛም ድንቅ ስራ እስከመጨረሻው የምንጸና ከሆነ ወንጌላችን በመላው ዓለም ይደረሳል ከዛም በእርግጥም ኢየሱስ ይመጣል የተስፋውንም ቃል ይጠብቃል! ከበደላችን ሁሉ ያነጻን እስካለንበት ጊዜ ድረስ በእምነት ያቆመን እግዚአብሔር ይመስገን እስከሞት ድረስት በሚታመን እምነትም ይባርከን! ወንድማችሁ Teferi Oshine Tanto Ethiopia/Hawassa

    • Teferi Oshine
    • Ethiopia
    • 05/10/202291
  • ቁ.5

    የእምነት ምስክርነት

    ሰላም ቅዱሳን ጸጋው የበዛላችሁ ከእግዚአብሔር የተሰጠን እውነተኛው ሰላም ከሁላችንም ጋር ይሁን! ዛሬ ከእምነት ምስክርነታችን እንድንማማር የእምነት ምስክርነቴን ልጽፍላችሁ ወደድኩ! እግዚአብሔር ቢፈቅድ በእምነት ህይወቴ የሚገጥሙኝን መልካምና ክፉ ገጠመኞቼን እንድንማርባቸው በቀጣይ ጊዜያት ልጽፍ እመኛለው!!! ዳግም መቼ እንደተወለድኩ ትክክለኛ ቀኑን ወሩንና አመቱን አላስታውስም!  ግን ጻድቅ ያደረገኝ እግዚአብሔር ይመስገን! እንዴት ዳግም እንደተወለድኩ ማብራራት እችላለው!  ከ6 አመቴ ጀምሮ እስከ 14 አመቴ ድረስ ያደኩት በፕሮቴስታንት ሀይማኖት ውስጥ ነበር! የውሃውን እና የመንፈሱን ወንጌል ለመጀመሪያ ጊዜ ከጎረቤት የሚኖር የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል አርበኛ ስራውን ሊሰራ የመንደሩን ህጻናት ሰበሰበ በሰዓቱ እኔ የ10 አመት ልጅ ነበርኩ!  ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እስከ 14 አመቴ በመንደራችን ከህጻናቱ ጋር ከአርበኛው የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እየሰማውና ቤተሰብ ከሚልከኝ ሀይማኖት ቤት በመጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ ስላሉ ነብያት ታሪክ እየተማርኩ ቀጠልኩ በ11 እና 12 ዓመቴ፣ የክርስቶስን ጽድቅ መሰረታዊ የድነት እውቀት እየለየው መጣው!  ያም የክርስቶስ ጽድቅ በልቤ እንዲታተም አደረገ ምስጋና ለመንፈስ ቅዱስ!!!  13 እና 14 አመት ሲሆነኝ የክርስቶስ ፅድቅ በልቤ ሲያብብ አየሁ!  ስለ ሰው ማንነት፣ ስለ ሕግ፣ ስለ መጥምቁ ዮሐንስ፣ ስለ ብሉይ ኪዳንኑና ስለ አዲስ ኪዳኑ የስርየት ሥርየት፣ ስለ ውኃ ደም መንፈስ መሠረታዊ የደኅነት እውቀትና በአጠቃላይ ስለ መንፈስ ቅዱስ ወንጌል የበለጠ ተረዳው።  ሳላስበው ወንጌልን ስሰብክ እና ውሸታሞችን እየተቃወምኩ የሬቨረንድ ፓውልሲ ጆንግን መጽሃፍ የማሰራጭ ሆኜ እያገለገልኩ መጣው!  ሀዋሪያው ጳውሎስ "እኔ ከሰበኩላችሁ ወንጌል ውጭ ማንም በሰብካችሁ የተረገመ ይሁን" ገላቲያ 1፥7-9  እንዳለው እኔም ከአውሃውና ከመንፈሱ ወንጌል ውጭ ሌላ ወንጌል ሁሉ ከሰይጣን መሆኑን የውሃውንና የመንፈሱ ወንጌል በመስበክ አረጋግጣለው! ወንጌላችን ሌላ አደለም (ኢየሱስ እንደመስዎዕቱ በግ ያለነውር ከሰማይ መቷል በእጆች መጫን ስርዓት በጥምቀቱ የዓለምን ሁሉ ሀጢአት ወስዷል ሰለሀጢአትም ዋጋን ሁሉ ከፍሏል በእርግጥም ሞቷል በሶስተኛውም ቀን ከሞት ተነስቷል የሚል ነው ሀሌሉያ!) በሚገርም ሁኔታ እዚሁ 14ኛ አመቴ ላይ እያለው ጥምቀት ምን ማለት እንደሆነ በደንብ ከተረዳው በኋላ ፕሮቴስታንቶች እድሜክ 14 ደርሷል ብለው የጥምቀት ትምህርት እንድጀምር ተነገረኝ! መንፈስ ቅዱስ ወደ ውቡ ወንጌል (የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል) ጠቅልሎ ሊወስደኝ ሲወድ ያንን አደረገ! እኔ ባህሪዬ ዝምተኛና አይንአፋር ነኝ¡ የዛን ቀን ግን በሙሉ ድፍረት የተለያዩ ጥያቄዎችንና ንግግሮችን ሳደርግ እንደነበር አስታውሳለው ከጥያቄዎቼ አንዱ ኢየሱስ ለምን ተጠመቀ? የሚል ነበር ምንም እንኳን ብዙ እና ከእኔ ትላልቅ ቢሆኑም ኢየሱስ ለምን እንደተጠመቀ አያውቁም ነበር በተዋቡ ቃላት የተሳሳቱ መልሶችን ብቻ ይመልሳሉ! በንግግራቸው ሁሉም እንደህጻናት ይታዩኝ ጀመር! ከዛን ጊዜ ጀምሮ በእኔ ላይ የተለያዩ ጥቃቶችን ማድረስ ጀመሩ ለጓደኞቼ በሙሉ ተፈሪ የስዕተት አስተምህሮት ውስጥ ገብቷል እርሱን እንዳትሰሙት የሚል ማስጠንቀቂያ ሰጡ! በዚህ ሁሉ ውስጥ መንፈስ ቅዱስ ድፍረት ሲሆነኝ እምነትን ሲሰጠኝ አንደበቶቼን ሲዳስስ እንደነበር አያለው፡ በመጨረሻም የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል አሸንፎ ሙሉ እኔነቴን ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል አቅርብያለው በድጋሚ ምስጋን ለመንፈስ ቅዱስ ይሁን!!! ከዛን ጌዜ ጀምሮ ሳልቀላቅል ከውሃውና ከመንፈሱ ወንጌል ውሃ ጣፍጦኝ እየጠጣው ነው! ውቡ ወንጌላችን በዓለም ሁሉ ይድረስ!!! ሁላችንም እስከሞት ድረስ በእምነታችን እንድንጸና አባታችን ኢየሱስ በነገር ሁሉ ይርዳን! ወዳችኋለው ተባረኩ! ወንድማችሁ ተፈሪ ኦሺኔ ታንቶ Ethiopia/Hawassa

    • Teferi Oshine
    • Ethiopia
    • 11/19/2021113
  • ቁ.4

    አሁን ግን ከዚህ የዲያብሎስ ሽንገላ ነጻ የሚያወጡበትና ከኃጢአት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የሚድኑበት ዘመን መጥቷል። 

    አያሌ ክርስቲያኖች ክርስቶስ በመስቀል ላይ እንደሞተላቸው ቢያምኑም፣ ግን ኃጢአተኞች ናቸው። ኢየሱስ የአዳምን ወይም የውርስ ኃጢአት ብቻ እንዳስወገደ ስለሚያምኑ፣ በየዕለቱ ለሚሰሩት ኃጢአት ስርየትን ለማግኘት በእ/ር ፊት ያለቅሳሉ። በክርስቶስ ቢያምኑም ኃጢአተኞች እንደሆኑ ያስባሉ። አሁን ግን ከዚህ የዲያብሎስ ሽንገላ ነጻ የሚያወጡበትና ከኃጢአት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የሚድኑበት ዘመን መጥቷል። Bereket Make Mara, Ethiopia

    • Bereket Make Mara
    • Ethiopia
    • 11/02/202149
  • ቁ.3

    የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ከሐጢያት አድኖኛል፡፡

    ከዓመታት በፊት በአንድ ቢሮ ውስጥ እየሰራሁ አንድ ወጣት ባለ ጉዳይ ወደ ቢሮዬ መጣ፡፡ በእጁ ‹‹Have You Truly Been Born Again of Water and The Spirit?›› የሚል በእንግሊዝኛ የተጻፈ መጽሐፍ ይዞ ነበር፡፡ ርዕሱ ትንሽ እንግዳ ስለሆነብኝ ወጣቱ የሚፈልገውን ካሰተናገድሁት በኋላ መጽሐፉን አየው ዘንድ ቢፈቅድልኝ ብዬ ጠየቅሁት፡፡ ወጣቱም ‹‹እንዲያውም ትርፍ ስላለኝ ውሰደውና አንብበው›› በማለት ሰጠኝ፡፡ በአክብሮት ተቀበልኩት፡፡ ወደ ቤት ከተመለስሁ በኋላ በመደርደሪያዬ ላይ አስቀመጥሁት፡፡ ለአንድ ሳምንት ያህል አላየሁትም፡፡    አንድ ቀን ሌላ መጽሐፍ ስፈልግ ዓይኖቼ በዚህ መጽሐፍ ላይ አረፉ፡፡ የምፈልገውን መጽሐፍ ትቼ ይህንን መጽሐፍ ከመደርደሪያው ላይ ሳብ አድርጌ እንደ ነገሩ ማገላበጥ ጀመርሁ፡፡ የአንድ መጽሐፍ ምንነት የሚታወቀው መቅድሙን በማንበብ እንደሆነ ስለማውቅ የዚህን መጽሐፍ መቅድም ማንበብ ጀመርሁ፡፡ ምንም እንኳን በሃይማኖት ቤት ለረጅም ጊዜ ባሳልፍም የኢየሱስ ጥምቀት ከደህንነቴ ጋር ይገናኛል ብዬ አንዴም እንኳን አስቤ አላውቅም ነበር፡፡  በእጄ ላይ ያለው መጽሐፍ ፈጽሞ አዲስ የደህንነት እሳቤን አሳየኝ፡፡ የኢየሱስ ጥምቀትና ዳግመኛ ከውሃና ከመንፈስ መወለድ ለእኔ ፈጽሞ አዲስ መገለጦች ነበሩ፡፡ ይህንን መጽሐፍ በታላቅ ጉጉትና አውቆ ለመዳን በተከፈተ ልብ ማንበቤን ተያያዘሁት፡፡ የብሉይ ኪዳን የመሥዋዕት ስርዓት፤ የእጆች መጫን፤ የመሥዋዕቶችን ደም የማፍሰስ ስርዓት በአዲስ ኪዳን ከኢየሱስ ጥምቀትና ሞት ጋር ያላቸውን ቁርኝት በሰፋት በተረዳሁ ጊዜ፤ ኢየሱስ የአዲስ ኪዳን የእግዚአብሄር በግ ሆኖ ወደዚሀ ምድር በመምጣት የሰው ዘር ወኪል (ዮሐንስ 11፡11) በሆነው በአጥማቂው ዮሐንስ አማካይነት ሐጢያቶቼን በሙሉ በራሱ ላይ በጥምቀቱ መወሰዱን ሳውቅና ይህም በጥላው ለመስዋዕቶች በሚቀርቡት እንስሶች ላይ በሚደረገው የእጆች መጫን ስርዓት አማካይነት ከሚተላለፉት የሐጢያተኛው ሐጢያቶች ጋር መሳ ለመሳ እንደሚመሳሰል ስረዳ ለዚህ ትልቅ የመዳን ዕውቀት እጄን ወደላይ አንስቼ ከመማረክ በቀር ላደርገው የምችለው ነገር አልነበረም፡፡ ይህ የእውነት ብርሃን በልቤ ላይ በራ፡፡ ሐጢያት አልባ ያደረገኝ የኢየሱስ ጥምቀትና የመስቀል ላይ ሞቱ ነፍሴን በሐሴት ሞላት፡፡ ኢየሱስ ተጠምቆ ‹‹ጽድቅን ሁሉ በመፈጸም›› (ማቴዎስ 3፡15) የዘላለም ጽድቁን ስላወረሰኝ አሁን ጻድቅ ነኝ፡፡ ዳግመኛ ከተወለድሁም 18 ዓመት አልፎኛል፡፡ አሁን የ18 ዓመት መንፈሳዊ ወጣት ነኝ፡፡ ይህንን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ገናም በሐጢያት እስራት ውስጥ ላሉና በጨለማ ውስጥ ለሚዳክሩ መስበኬን አላቋረጥሁም፡፡ ክብር በውሃ፣ በደምና በመንፈስ (1ኛ ዮሐንስ 5፡6) ለመጣው፣ ሐጢያቴን ከላዬ ላይ እንዳረጀ  ልብስ ገፎ ለጣለውና አዲሱን የጽድቅ ልብስ ላለበሰኝ ለኢየሱስ ክርስቶስ ይሁን! አሜን!! ካሳሁን አየለ, Ethiopia

    • Kassahun Ayele
    • Ethiopia
    • 10/31/202135