Search

በነጻ የሚታደሉ የታተሙ መጽሐፎች፣
ኢመጽሐፎችና የኦዲዮ መጽሐፎች፤

የማቴዎስ ወንጌል፤

በማቴዎስ ወንጌል ላይ የተሰጡ ስብከቶች (IV) - ኢየሱስ የሰጠን መንፈሳዊ በረከቶች
  • ISBN9788928241408
  • ገጾች፤290

አማርኛ 30

በማቴዎስ ወንጌል ላይ የተሰጡ ስብከቶች (IV) - ኢየሱስ የሰጠን መንፈሳዊ በረከቶች

Rev. Paul C. Jong

የማውጫ ሰሌዳ 
 
መቅድም 

ምዕራፍ 21
1. እግዚአብሄር የሚጠቀምባቸው ሠራተኞች (ማቴዎስ 21፡1-11) 
2. በጌታ ሥራ ውስጥ ማገልገል ክብር ነው (ማቴዎስ 21፡1-11) 
3. ‹‹ለጌታ ያስፈልጉታል›› በሉ (ማቴዎስ 21፡1-14) 
4. በመጀመሪያና በቅድሚያ እግዚአብሄርን ውደዱ (ማቴዎስ 21፡12-32) 
5. በአጥማቂው ዮሐንስ ሥራና ለሐጢያቶቻችን በሆነው የስርየት ወንጌል መካከል ያለው ዝምድና (ማቴዎስ 21፡32) 
6. እግዚአብሄርን የሚቃወመው የሰው አስተሳሰብ (ማቴዎስ 21፡44) 
7. ፈላስፋውያን አገልጋዮች የኢየሱስን ወንጌል ይቃወማሉ (ማቴዎስ 21፡44) 

ምዕራፍ 22
1. በሰማይ ባለው ድግስ ላይ ሊገኙ የሚችሉት የውሃውንና የደሙን ልብስ የለበሱ ሰዎች ብቻ ናቸው (ማቴዎስ 22፡1-14) 
2. የሠርጉ ድግስ ምሳሌ (ማቴዎስ 22፡1-14) 
3. የሐጢያቶችን ስርየት ልብስ ልበሱ (ማቴዎስ 22፡1-14) 

ምዕራፍ 23
1. ግብዝና ዕውር መሪዎች (ማቴዎስ 23፡1-33) 

ምዕራፍ 24
1. አሁኑኑ ለጌታ ዳግመኛ ምጽዓት የተዘጋጀ እምነት ይኑራችሁ (ማቴዎስ 24፡1-8) 
2. ለፍጻሜዎቹ ዘመናት ተዘጋጁ (ማቴዎስ 24፡3-14) 
3. እስከ መጨረሻው ድረስ ታማኝ ሠራተኞች እንሁን (ማቴዎስ 24፡3-14) 
 
እኛ እያሰራጨነው ባለነው የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል በማመን ዳግም የተወለዱ በርካታ አዳዲስ ክርስቲያኖች በመላው አለም አሉ፡፡ እኛ በእርግጥም ለእነርሱ የሕይወት እንጀራን ልንመግብ እንናፍቃለን፡፡ ነገር ግን ከእኛ በጣም ርቀው ያሉ በመሆናቸው በእውነተኛው ወንጌል ከእነርሱ ጋር ሕብረት ማድረግ አስቸጋሪ ነው፡፡
ስለዚህ የእነዚህን የነገስታት ንጉስ የሆነው የኢየሱስ ክርስቶስ ሕዝቦች መንፈሳዊ ፍላጎቶች ለማሟላት ደራሲው በኢየሡስ ክርስቶስ ቃል በማመን የሐጢያቶቻቸውን ስርየት የተቀበሉ ሰዎች እምነታቸውን ለመከላከልና መንፈሳዊ ሕይወታቸውን ለመደገፍ ንጹሕ የሆነውን የእርሱን ቃል መመገብ እንዳለባቸው ይናገራል፡፡ በእነዚህ መጽሐፎች ውስጥ ያሉት ስብከቶች መንፈሳዊ ዕድገታቸውን ለማነጽ ሲባል ዳግም የተወለዱትን የሚመግቡ ትኩስ የሕይወት እንጀራ ሆነው ተዘጋጅተዋል፡፡
እግዚአብሄር በቤተክርስቲያኑና በአገልጋዮቹ አማካይነት ይህንን የሕይወት እንጀራ በማቅረብ ይቀጥላል፡፡ የእግዚአብሄር በረከቶች ከውሃውና ከመንፈሱ ወንጌል ዳግም በተወለዱና ከእኛም ጋር በኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ መንፈሳዊ ሕብረት እንዲኖራቸው ከሚሹ ሰዎች ሁሉ ጋር ይሁኑ፡፡
ኢመጽሐፍ አውርድ፤
PDF EPUB