Search

በነጻ የሚታደሉ የታተሙ መጽሐፎች፣
ኢመጽሐፎችና የኦዲዮ መጽሐፎች፤

የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል፤

በውኑ በውሃውና በመንፈሱ ዳግም ተወልዳችኋልን?
  • ISBN8983147512
  • ገጾች፤392

አማርኛ 1

በውኑ በውሃውና በመንፈሱ ዳግም ተወልዳችኋልን?

Rev. Paul C. Jong

ማውጫ
 
መቅድም 
 
ክፍል አንድ—ስብከቶች 
1. ለመዳን አስቀድመን ስለ ሐጢያቶቻችን ማወቅ አለብን (ማርቆስ 7፡8-9,20-23) 
2. ሰዎች ሐጢያተኞች ሆነው የተወለዱ ናቸው (ማርቆስ7፡20-23) 
3. ነገሮችን በሕጉ መሰረት ብናደርግ ሕጉ ሊያድነን ይችላልን? (ሉቃስ10፡25-30) 
4. ዘላለማዊ ቤዛነት (ዮሐንስ 8፡1-12) 
5. የኢየሱስ ጥምቀትና የሐጢያቶች ስርየት (ማቴዎስ 3፡13-17) 
6. ኢየሱስ ክርስቶስ የመጣው በውሃ፣ በደምና በመንፈስ ነው (1ኛ ዮሐንስ 5፡1-12) 
7. የኢየሱስ ጥምቀት ለሐጢያተኞች የደህንነት ምሳሌ ነው (1ኛ ጴጥሮስ 3፡20-22) 
8. የተትረፈረፈው የስርየት ወንጌል (ዮሐንስ 13፡1-17) 

ክፍል ሁለትአባሪ 
1. የደህንነት ምስክርነቶች 
2. ተጨማሪ ማብራሪያ 
3. ጥያቄዎችና መልሶቻቸው 
 
የርዕሱ ዋናው ጉዳይ ‹‹ከውሃና ከመንፈስ ዳግመኛ መወለድ›› ነው፡፡ ይህ ጉዳይ ለየት ያለ ርዕስ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ይህ መጽሐፍ ዳግመኛ መወለድ ምን እንደሆነና ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር በጥብቅ በተስማማ መልኩ እንዴት ከውሃና ከመንፈስ መወለድ እንደሚቻል በግልጽ ይነግረናል፡፡ ውሃው በዮርዳኖስ የሆነውን የኢየሱስ ጥምቀት ያመለክታል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ በተጠመቀ ጊዜ ሐጢያቶቻችን በሙሉ ወደ ኢየሱስ እንደተላለፉ ይናገራል፡፡ ዮሐንስ የሰው ዘር ሁሉ ወኪልና የሊቀ ካህኑ የአሮን ዘር ነው፡፡ አሮን በስርየት ቀን በሚለቀቀው ፍየል ራስ ላይ እጆቹን ጫነና የእስራኤላውያንን አመታዊ ሐጢያቶች በሙሉ በእርሱ ላይ አስተላለፈ፡፡ ይህ ሊመጡ ያሉ ነገሮች ጥላ ነበር፡፡ የኢየሱስ ጥምቀት የእጆች መጫን ምሳሌ ነው፡፡ ኢየሱስ በዮርዳኖስ በእጆች መጫን መልክ ተጠመቀ፡፡ ስለዚህ በጥምቀቱ አማካይነት የአለምን ሐጢያቶች በሙሉ ወሰደና ለሐጢያቶች ዋጋ ለመክፈልም ተሰቀለ፡፡ የዚህ መጽሐፍ ቁልፍ ቃል የኢየሱስ ጥምቀትና የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል አስፈላጊ ክፍል ነው፡፡ ዳግመኛ ልንወለድ የምንችለው በኢየሱስ ጥምቀትና በመስቀሉ ስናምን ብቻ ነው፡፡
ኢመጽሐፍ አውርድ፤
PDF EPUB
በነጻ የሚታደል የታተመ መጽሐፍ፤
ይህንን የታተመ መጽሐፍ ጋሪው ላይ ጨምር፤
ኦድዮ መጽሐፍ፤
ኦድዮ መጽሐፍ፤

ከዚህ ርዕሰ ጋር የተዛመዱ መጽሐፎች